Tender Detail

Tender Details


የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በ2019 በጀት ዓመት ለክርስትና እምነት ተከታዮች የዳልጋ ከብት ሥጋ መሸጫ እና የበግና ፍየል ሥጋ መሸጫ የሚሆን እንዲሁም ለእስልምና እምነት ተከታዮች የበግና ፍየል ሥጋ መሸጫ የሚሆን የተለያዩ ሱቆችን /ኮንቴይነሮችን/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡


የሥጋ መሸጫ ሱቆች ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በ2019 በጀት ዓመት ለክርስትና እምነት ተከታዮች የዳልጋ ከብት ሥጋ መሸጫ እና የበግና ፍየል ሥጋ መሸጫ የሚሆን እንዲሁም ለእስልምና እምነት ተከታዮች የበግና ፍየል ሥጋ መሸጫ የሚሆን የተለያዩ ሱቆችን /ኮንቴይነሮችን/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ ማንኛውም ተጫራች፡-

  • በመስኩ ወይም በተመሳሳይ ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ያለውና የዘመኑ ግብር የከፈለ የማይመለስ ኮፒ በማያያዝ ማቅረብ አለበት፡፡
  • የጨረታ ማስከበሪያ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀዉ መሰረት ይሆናል፡፡
  • የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ማርኬቲንግ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ መውሰድ ይችላል፡፡
  • የዋጋ ማቅረቢያና ሌሎች መረጃዎች የያዘውን የጨረታ ሠነድ በታሸገ ኢንቨሎፕ ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በፊት በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ማስገባት አለበት፡፡
  • ጨረታው ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት በ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ውስጥ ይከፈታል፡፡
  • ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

ለተጨማሪ ማብራሪያ በ8868/ 0114163978/ ይጠይቁ፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት

Save Tender