አፈጻጸም ክርክር አስመልክቶ በቢሾፍቱ ከተማ ዲባዩ ክፍለ ከተማ ደካ ቦራ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ 2 የግል መኖሪያ ቤቶችን የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በጨረታ ለመሸጥ ስለሚፈልግ ይህን መኖሪያ ቤት በጨረታ ለመግዛት የሚፈልጉ ሰዎች ወይም አካላት እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍርድ ባለመብት አቶ ሀይሉ ጉልማ እና በፍርድ ባለእዳ ወ/ሮ ሀረጓ አደም መካከል ያለውን የፍርድ አፈጻጸም ክርክር አስመልክቶ በቢሾፍቱ ከተማ ዲባዩ ክፍለ ከተማ ደካ ቦራ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ፣ ስፋቱ 500 (አምስት መቶ) ካሬ ሜትር የሆነ በቢሾፍቱ ከተማ የመሬት አስተዳደር ተመዝግቦ ያለ፣ ወሰኑ በምስራቅ መንገድ በምዕራብ መንገድ በሰሜን የግል መኖሪያ ቤት እና በደቡብ በመንገድ የታጠረ በሟች አቶ ጉልማ ደባቡ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ግምቱ ብር 3,138,179.70 (ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ሰባ ዘጠኝ ከሰባ ሳንቲም) የሆነን መኖሪያ ቤት የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በጨረታ ለመሸጥ ስለሚፈልግ ይህን መኖሪያ ቤት በጨረታ ለመግዛት የሚፈልጉ ሰዎች ወይም አካላት የጨረታውን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4) በሲፒኦ (CPO) በማስያዝ ጨረታው በሚካሄድበት ቀን 05/10/2018 ዓ ም. ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ 6:30 ሰዓት ድረስ ጨረታው በሚካሄድበት በቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ተወዳድረው እንዲገዙ የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት አዟል፡፡
በቢሾፍቱ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዲባዩ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት
