ድርጅታችን ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር የኮንስትራክሽን ዕቃዎች, ያገለገሉ አርኤችኤስ,E አዲስ ስፔር ፓርት መለዋወጫ ዕቃዎች, አዳዲስ የባንባ ዕቃዎች, በሚገኙበት በ ገላን ከተማ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቅያ
ድርጅታችን ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር የኮንስትራክሽን ዕቃዎች, ያገለገሉ አርኤችኤስ,E አዲስ ስፔር ፓርት መለዋወጫ ዕቃዎች, አዳዲስ የባንባ ዕቃዎች, በሚገኙበት በ ገላን ከተማ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ተጫራቶች የሚጫረቱትን ንብረት ይህ ጨረታ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 8 ተከታታይ የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከድርጅታችን ዋና ቢሮ 2ኛ ፎቅ ፋይናንስ ክፍል የማይመለስ ብር 300 በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቶች ንብረቱ በሚገኘው ገላን ከተማ ቀርበው መመልከት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም በጨረታው ላይ የሚሳተፋ ተጫራቶች የተጠቀሱት ንብረቶች የጨረታው ማስከበሪያ (Bid Bond) ከምታቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 5% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የባንክ ጋራንቲ ከዋናው ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ በጨረታ ዶክመንት ዉስጥ በተዘጋጀዉ የማጫረቻ ዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ በመሙላት በታሸገ ፖስታ ዉስጥ አስገብተዉ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀዉ ሳጥን ዉስጥ ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን 16/9/2018 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት ቅዳሜን ጨምሮ 8 ተከታታይ የስራ ቀናት ዉስጥ ዋናዉ መ/ቤት መግቢያ ላይ ባለዉ የእንግዳ መቀበያ አጠገብ በተቀመጠዉ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታዉ በቀን 25/9/2018 ዓ/ም ማክሰኞ 11፡00 ሰአት ይዘጋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቶች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅታችን ዋና መ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በቀን 26/9/2018 ዓ/ም ሮብ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ይከፈታል፡፡ ተጫራቶች ወይም ወኪሎቻቸው ካልተገኙ ጨረታው በጨረታ ኮሚቴና ታዛቢ ባሉበት የሚከፈት መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- ተጫራቶች የሚያቀርቡት ዋጋ ተ/እ/ታ /VAT/ ያካተተ መሆን ይኖርበታል፡:
- ተጫራቶች ያስያዙት ሲፒኦ ካቀረቡት ዋጋ አንሶ ከተገኘ ከጨረታው ይሰረዛሉ፡፡
- የመጫረቻ ዋጋ ቅፅ ላይ ሲሞላ ስርዝ ድልዝ እና አሻሚነት ያለው የቁጥር አፃፃፍ ተቀባይነት የለውም፡፡
- የጨረታው አሸናፊዎች ማሸነፋቸው ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ ባሎት 5 ቀናት ውስጥ ክፍያውን ሙሉ በሙሉ ከፍለው ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊዎች ክፍያ ከፈፀሙ በ10 ቀናት ውስጥ በራሳቸው ትራንስፖርትና ወጪ ንብረቱን ሙሉ በሙሉ ማንሳት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊዎች ክፍያ በተቀመጠው በ5 ቀናት የጊዜ ገደብ ካልከፈለ ጨረታው ውድቅ ሆኖ ለጨረታው ያስያዙት /bid bond/ ተመላሽ አይደረግም፡፡
- በጨረታው ተሳታፊ ሆነው ጨረታውን ላላሸነፋ ተጫራቶች ለጨረታው ያስያዙት (Bid Bond) ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ
አድራሻ፡– ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ. የተ. የግል ማህበር
ቫቲካን ፊት ለፊት ያለው መርየም ህንፃ እንገኛለን
የስልክ ቁጥር 0115573196/0115573198
ፋክስ 0115573187/0115573197
ኢ-ሜይል yotekconplc@gmail.com
አዲስ አበባ
