በቤንቾ ሸኮ ቦን የሰሜን ቤንች ወረዳ ስጌንጃ ታዳጊ ማዘጋጃ በደ.ቁ.ፕጌታማ 02/526 በቀን 14/08/2018 ዓ.ም ስጌንጃ ታዳጊ ማዘጋጃ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ኮረት ማጓጓዝ ጠጠር ወስዶ የመድሩት እና የመበተን እና ቦይ የማውጣት ስራ ለማሰራት የሲኖ ገልባጭ መኪና (Damp Truck) እና (የግሬደር ማሽን) ይፈልጋል።
በድጋሚ ለ2ዙር የወጣ ለጌንጃ ታዳጊ ማዘጋጃ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ኮረት ማጓጓዝ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው በቤንቾ ሸኮ ቦን የሰሜን ቤንች ወረዳ ስጌንጃ ታዳጊ ማዘጋጃ በደ.ቁ.ፕጌታማ 02/526 በቀን 14/08/2018 ዓ.ም ስጌንጃ ታዳጊ ማዘጋጃ ውስጥ ለውስጥ መንገድ ኮረት ማጓጓዝ ጠጠር ወስዶ የመድሩት እና የመበተን እና ቦይ የማውጣት ስራ ለማሰራት የሲኖ ገልባጭ መኪና (Damp Truck) እና (የግሬደር ማሽን) ጨረታ እንድናወጣ ጠይቀውናል፡፡ በጠየቁን መሰረት ይህን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሠስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ጨረታውን መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
በዚሁም መሰረት፡-
1. በዘርፉ የስራ መስከ የተሰማሩበትን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
2. ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣ የንግድ ፍቃድ ያለውና ፍቃዳቸውን ያሳደሱበት የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
3. የቲን ነምበር ማስረጃ እና ተጨማሪ እሴት ታከስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
4. የሲኖ ገልባጭ መኪና እና የግሬደር ማሽን ሊብሬ የሁለቱንም ሊብሬ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
5. የመድን ዋስትና (ሶስተኛ ወገን) ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
6. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ CPO ብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
7. ተጫራቾች ጨረታውን ተወዳድራችሁ ካለፋችሁ የመጀመሪያ ዙር ክፍያ የሚጠይቁ ከሆነ ለክፍያው ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሽያጭ ሰ/ቤ/ወ/ገቢዎች ቅ/ጽ/ቤት ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ሰ/ቤ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 በመገኘት መውሰድ ትችላላችሁ።
9. ተጫራቾች የተጠየቁትን መስፈርቶች 1 /አንድ/ ኦርጅናል 2 /ሁለት/ ኮፒ በማድረግ በተለያዩ 3 ፖስታዎች በማሸግ ሰ/ቤ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
10. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዱ ላይ ህጋዊ ማህተማቸውንና ፊርማቸውን ማስፈር ይጠበቅባቸዋል በተጨማሪም ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡
11. ጨረታው የሚታሸገ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ወይም በአየርላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀን አየር ላይ ውሎ በሰ/ቤንች ወረዳ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸ በተገኙበት ታሸጎ ልክ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካዮቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ባይገኙም አንገደድም።
ማሳሰቢያ፡- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0948950573/0946521985/0935170895/ ይደውሉ፡፡
በደ/ም/ኢት/ህ/ክ/መንግስት በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት
