የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የቀረበውን ለ2ኛ ዙር የወጣ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ዙር የወጣ ኤሌክትሮኒክስ ግዥ
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 456/2018
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የቀረበውን ለ2ኛ ዙር የወጣ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
መለኪያ
|
ብዛት
|
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚከፈትበት ሰዓት
|
መክፈቻ ቦታ
|
|
1
|
ኤሌክትሮኒክስ
|
በቁጥር
|
25
|
200,000
|
በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡10 ይከፈታል |
ዲላ መምህራን ኮሌጅ ግቢ (ግብርና ቢሮ) ግዥ ን/እስ ዳይሬክቶሬት ክፍል |
በመሆኑም በንግድ ሥራ ዘርፉ የታደሰ ፈቃድ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸውና የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸውና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል። በተጫራቾች የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ያስያዙበትን ማቅረብ አለባቸው።
ተጫራቾች በቢሮው የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጠበት ቀን ጀምሮ ባለው ተከታታይ 15 ቀናት እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 300.00(ሶስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል በዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ትትስ ግቢ ከሚገኘው የመ/ቤቱ የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
· ተጫራቾች የመጫረቻ ሠነድ በመሙላት ይህ የጨረታ የቴክኒካልና ፋይናንሻል ኦርጅናልና አንድ ኮፕ የማጫረቻ ሰነዶችን በአንድ እናት ፖስታ በማዘጋጀት በ16ኛው ቀን በቢሮው ግዥና ንብ/አስ/ዳይ/ቢሮ ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። እንዲሁም ተጫራቾች / ተወካዮቻቸው/ በተገኙበት በቢሮው የግዥና ንብ/አስ/ዳይ/ቢሮ ይከፈታል።
· ቢሮው በቀረበው ጨሪታ ላይ ከአሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈራረሙ በፊት የግዥውን 20 ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል።
· ከ200,000 ሺህ በላይ ለሆኑ ግዥዎች ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
· የጨረታው ሳጥን መክፈቻ በ16ኛው ቀን የመንግስት የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በቀጣይ ባለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
· ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 046 131 0134 ይጠቀሙ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ
