በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ውርስ ሆኖ በመጋዘን የሚገኝ የተለያዩ ሞባይል ቀፎዎች እና ቴሌቪዥኖችን በሀራጅ ጨረታ ባለበት ሁኔታ በኦላይን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
ኦላይን የሐራጅ ጨረታ ቁጥር AE01/2018
በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ውርስ ሆኖ በመጋዘን የሚገኝ የተለያዩ ዕቃዎች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሀራጅ ጨረታ ባለበት ሁኔታ ኦላይን አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት ፡-
በግልጽ ጨረታ ቁጥር AE01/2018 በ11/10/2018 የተለያዩ ሞባይል ቀፎዎች፣ ቴሌቪዥን በኦላይን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች
1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመነ ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት የተሠጠ ማስረጃ እና መለያ ቁጥሩን በኦላይን ማቅረብ የሚችል መሆኑን ይጠበቅበታል፡፡
2. ለጨረታ የሚቀርቡ ዕቃዎች የሚገኙት በድሬዳዋ ሙድአነኖ ግቢ ውስጥ በሚገኘው የውርስ ዕቃ መጋዘን ውስጥ ነው።
3. በሐራጅ ጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ላይ በተጠቀሰው ቀን መሰረት በኦላይን ብር 100 በመግዛት ጨረታ ላይ መሳተፍ ይቻላል፡፡ የዕቃዎችን ሳንፕል በኦላይን መገኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ እቃዎቹን ሳያዩ ዋጋ ሰጥቶ ለሚፈጠረው ችግር ቅ/ጽ/ቤቱ ተጠያቂ አይሆንም፡፡
4. ጨረታው የሚካሄደው በኦንላይን ነው።
5. ለሐራጅ ጨረታ ለሽያጭ የቀረቡት እቃዎች በኮድ የተከፋፈለ ሲሆን ተጫራቾች የሚሰጡት ዋጋ ከቫት በፊት መሆን አለበት፡፡
6. ተጫራች በሀራጅ ጨረታ ለመጫረት ለአያንዳንዱ ኮዶች የተቀመጠውን ለጨረታው ዋስትና ማስከበሪያ ዋጋ 5% በ(Tele birr)፤ Auction Ethiopia ወይንም በባንክ (ንግድ ባንክ) የተረጋገጠ (CPO) በድሬዳዋ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ስም ማሰራት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ተጫራቾች በአንላይን ሀራጅ ጨረታ ኦንላይን ከሆነበት ከ04/10/2018 4:00 ሰአት ጀምሮ እስከ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን 11/10/2018 4፡00 ሰአት መሳተፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. በጨረታው አሸናፊ የሆነ ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ያስያዘው ሲፒኦ ከሚከፍለው ዋጋ ጋር የሚታሰብ ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ ሲፒኦ በሀርድ ኮፒ የተሰራ ከሆነ በሶስት የስራ ቀናቶች ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
9. አሸናፊ የሆነ ተጫራች የተወዳደረበትን እቃዎች አሸናፊ ስለመሆኑ በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ቀናቶች ውስጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ንብረቱን መረከብ ይኖርበታል፡፡
10. ከላይ በተራ ቁጥር 9 ላይ በተገለጸው ቀናቶች ውስጥ ክፍያውን ፈጽሞ ዕቃውን ያልተረከበ በተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘውን ሲፒኦ ለባለስልጣኑ መ/ቤት ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለጨረታ የሚቀርብ መሆኑን እንገልፃልን፡፡
11. የጉምሩክ ኮምሽን ቅ/ጽ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር ፡- 0915460970 (0912885746) መደወል ይቻላል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት
