የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሐረሪ ሪጅን ከዚህ ስር ያሉትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር:- EEU/S.C&PGS/NCB-009/2018
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሐረሪ ሪጅን ከዚህ ስር ያሉትን ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
የሚወገደው ንብረት ዓይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒአ |
የጨረታው መዝጊያ እና መከፈቻ ቀን |
|
1 |
የተለያዩ መጠን ያላቸው የሚወገዱ ንብረቶች |
የተለያዩ መጠን ያላቸው የተሸፈኑ አልሙኒየም እና ያልተሸፈኑ አልሙኒየም ኬብሎች |
46,102.00 |
|
|
የተለያዩ ከአገልግሎት የተመለሱ ብረታ ብረቶች |
መከፈቻ:- ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 4:30 |
|||
|
የተለያዩ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማዎች |
||||
|
የተለያዩ ያገለገሉ የትራንስፈርመር ዘይት በርሜሎች |
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
1. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ 300(ሶስት መቶ) ብር ዘወትር በስራ ሰዓት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሐረሪ ሪጅን ፅ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 207 በመምጣት የሚወገዱ ንብረቶች ዝርዝር መረጃ የያዘ የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት፤ ከሰአት በኋላ ከቀኑ 7፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹ ባሉበት ቦታ በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በባንክ በተረጋገጠ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን እና የጨረታ ማስከበሪያቸውን በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ስማቸውን እና የጨረታ ቁጥር EEU/S.C&PGS/NCB-009/2018 በመግለፅ ከላይ በተገለፀው ቀን እና ሰዓት ድረስ ብቻ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
5. ጨረታው ከላይ በተጠቀሱት ቀንና ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም ሐረር ራስ ሆቴል ጀርባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት ሐረሪ ሪጅን ፅ/ቤት 2ኛ ፎቅ ሰፕላይቼን እና ፕሮፐርቲ ጀነራል ሰርቪስ ቢሮ ቁጥር 207 ይከፈታል፡፡
6. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ተጨማሪ እሴት ታከስን ጨምሮ መሆን አለበት።
7. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 025-466-3575 መደወል ይችላሉ፡፡
8. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሐረሪ ሪጅን
