የምሥራቅ ሐረርጌ ማረሚያ ቤት በሐረር ለሚገኙ ለሕግ ታራሚዎች ቀለብ አገልግሎት የሚውል የበሰለ ምግብ ጥራቱን የጠበቀ ለአንድ ሰው በቀን 40.60(አርባ ብር ከስልሳ ሳንቲም) በቀን ተሰልቶ የሚከፈል ቁርስ፣ ምሳ፣እራት እንዲሁም ለምግብ ማብሰያ የሚውል መብራት፣ ውሃ፣ የማገዶ እንጨት እና የተለያዩ የጉልበት ሠራተኞች ከፍያ ዋጋ ተካቶበት ማቅረብ ለሚችሉ ጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራትን በጨረታ አወዳድሮ ከሐምሌ/1/2018 ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/10/2019 ለአንድ ዓመት የበሰለ ምግብ ማቅረብ ለሚችሉ ማኀበራት የወጣ ጨረታ፡፡
የበሰለ ምግብ ለሕግ ታራሚዎች ማቅረብ ለሚችሉ ለጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የምሥራቅ ሐረርጌ ማረሚያ ቤት በሐረር ለሚገኙ ለሕግ ታራሚዎች ቀለብ አገልግሎት የሚውል የበሰለ ምግብ ጥራቱን የጠበቀ ለአንድ ሰው በቀን 40.60(አርባ ብር ከስልሳ ሳንቲም) በቀን ተሰልቶ የሚከፈል ቁርስ፣ ምሳ፣እራት እንዲሁም ለምግብ ማብሰያ የሚውል መብራት፣ ውሃ፣ የማገዶ እንጨት እና የተለያዩ የጉልበት ሠራተኞች ከፍያ ዋጋ ተካቶበት ማቅረብ ለሚችሉ ጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራትን በጨረታ አወዳድሮ ከሐምሌ/1/2018 ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/10/2019 ለአንድ ዓመት የበሰለ ምግብ ማቅረብ ለሚችሉ ማኀበራት የወጣ ጨረታ፡፡
- ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ ሆኖ የከፈለበትን ማስረጃ ኦርጅናልና ኮፒ ማቅረብ የሚችል።
- ለሚከፈለው ገንዘብ ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
- የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 50 ( ሀምሳ ብር) በመከፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከዞኑ ማረሚያ ቤት በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በዞኑ ማረሚያ ቤት ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 80,000.00 ብር በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተመሰከረለት ቼከ cpo ጨረታው ላይ ማቅረብ አለበት፡፡
- ጨረታው በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ቀናት አየር ላይ ከቆየ በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 3:30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት በማረሚያ ቤት ውስጥ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኮሚቴ ባሉበት እና የመ/ቤቱ ኮሚቴ ባለበት ጨረታው በይፉ ይከፈታል፡፡ ዕለቱ በዓል ከሆነ በተከታዩ የሥራ ቀን ይከፈታል።
- ማረሚያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- መ/ቤቱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ውሉን የመሰረዝም ሆነ የማቋረጥ መብት አለው።
- ምግብ የሚበስለው በማረሚያ ቤት ውስጥ በተዘጋጀው ማብሰያ ቤት ውስጥ ሆኖ የማብሰያ ዕቃ የመሥሪያ ቤቱ እንዳለ ሆኖ የጎደለውን ዕቃ ባለቤቱ ማቅረብና ማሟላት የሚችል · መሆን አለበት።
- የምግብ እህልና ማጣፈጫዎችን ሚኖ ላይ በተቀመጠው መሠረት ማቅረብ ወይም መመግብ የሚችል መሆን አለበት።
ተጨማሪ መረጃ በሰልክ ቁጥር 0256660866/0256661619 ሞባይል 0915054945/091032905 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ማረሚያ ቤት
