ኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር ለምርት ሥራ አገልግሎት የሚውል Maize flour(Fine) በሀገር ውስጥ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር
WVD34/2018-09
1) ኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ አክሲዮን ማህበር ለምርት ሥራ አገልግሎት የሚውል Maize flour(Fine) በሀገር ውስጥ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
2) በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ከአክሲዮን ማህበሩ ቅ/ጽ/ቤት አዲስ አበባ ወይንም ከዋናው መሥሪያ ቤት ኮምቦልቻ መግዛት ይቻላል። ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በትከከል በመሙላት በሰም በታሸገ ፖስታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በጨረታ መመሪያው ላይ የተገለጸውን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ በ (CPO) ወይንም በባንክ ጋራንቲ በማስያዝ ኮምቦልቻ ዋናው መ/ቤት ወይም አዲስ አበባ ቅ/ጽ ቤት ፓፓሊኖስ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 143 ወይም 144 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ማቅረብ ይችላሉ።
3) ጨረታው ማስታወቂያው በተዘጋ በ3ኛው ቀን ኮምቦልቻ (ወሎ) በዋናው መሥሪያ ቤት ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
4) ይህ ቀን የሕዝብ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል።
5) አ/ማህበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን መሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ::
ስተጨማሪ ማብራሪያ
ስልክ ቁጥር -033-5510627/5510211/0973424242 (ኮምቦልቻ)
ስልክ ቁጥር- 011-5530124/5513797/0970230571 (አዲስ አበባ)
ራስ ደስታ ዳምጠው ጎዳና ፓፓሲኖስ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ
የኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማህበር
