በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት በዲንዲን፣ ጄሎ መክታር፣ ጋረ ሙለታ እና ጃርሶ ጉርሱም ዲስትሪክት የሚገኘውን የቁም ባህርዛፍ ግንድላ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የቁም ደን ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ OFWEDH/GU03/2018
በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት በዲንዲን፣ ጄሎ መክታር፣ ጋረ ሙለታ እና ጃርሶ ጉርሱም ዲስትሪክት የሚገኘውን የቁም ባህርዛፍ ግንድላ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም፡-
1. የግንድላ እና የአጠና፣ የእንጨት መሰንጠቂያ ወይም ተዛማች ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ እና “TIN number” ያላቸው ግለሰቦች፣ ድርጅቶች እና ማህበሮች እንዲሁም ስለጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፅ የጨረታ ሰነድ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ጭሮ ከተማ ምዕ/ሐርረጌ ዞን ውሃ እና ኢነርጂ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ከሐርረጌ ቅ/ጽ/ቤት ቁጥር 2 በመግዛት በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
2. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
3. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ትክክለኛው ቀንና ሰአት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለጻል።
4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት ጭሮ ከተማ ውስጥ በሚገኙት ባንኮች በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0920911314/0913551405 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሐረርጌ ቅርንጫፍ
