አማራ ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ከዚህ ቀጥሎ የቀረበውን ንብረት በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የሐራጅ ማስታወቂያ ቁጥር አማራ ባንክ 42/2018
አማራ ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ከዚህ ቀጥሎ የቀረበውን ንብረት በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
ንብረት አስያዥ |
አበዳሪው ቅርንጫፍ |
የንብረቱ አድራሻ |
የቦታው ስፋት |
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር |
የንብረቱ ዓይነት/የይዞታው አገልግሎት |
የጨረታ መነሻ ዋጋ /ብር/ |
ጨረታው የሚከናወንበት ቀን |
||||||
|
ቀን |
ሰዓት |
ቦታ |
|||||||||||||
|
ክ/ከተማ |
ከተማ |
ወረዳ |
ቀበሌ |
||||||||||||
|
1 |
ሲሳይ አስንቆ ከበደ |
ሲሳይ አሰንቆ ከበደ |
ቦሌ ፍላሚንጎ |
አቃቂ ቃሊቲ |
አዲስ አበባ |
04 |
- |
75.59 ካሬ ሜትር |
AA00007 0405714 1670323 |
መኖሪያ (ኮንዶሚንየም) |
4,052,295.39 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ዋና መሥሪያ ቤት 18ኛ ወለል |
|
|
2 |
ፀጋዬ ገላና ሀ/ማርያም |
ፀጋዬ ገላና ሀ/ማርያም |
ወሊሶ |
- |
ወሊሶ |
- |
02 |
200 ካሬ ሜትር |
W/4155/99 |
መኖሪያ |
2,883,054.26 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ4፡00 እስከ 5፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ዋና መሥሪያ ቤት 18ኛ ወለል |
|
|
3 |
መስፍን መንግሥቴ ውድነህ |
መስፍን መንግሥቴ ውድነህ |
ባህርዳር |
ግንቦት 20 |
ባህርዳር |
- |
14 |
3,000 ካሬ ሜትር |
32541/2010 |
ለኢንዱስትሪ |
41,996,341.54 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ባህር ዳር ዲስትሪክት ቢሮ |
|
|
እታገኘሁ ሁነኛው |
ባህርዳር |
ጣና |
ባህርዳር |
- |
16 |
244 ካሬ ሜትር |
16411/98 |
መኖሪያ |
7,745,444.22 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ4፡00 እስከ 5፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ባህር ዳር ዲስትሪክት ቢሮ |
|||
|
4 |
ምድረ ፈውስ የቅባትና የጥራጥሬ እህሎች ላኪነት ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
ዶ/ር መላኩ የኔነህ ፈንታ |
ፍኖተ ሰላም |
- |
ፍተኖተ ሰላም |
- |
02 |
622 ካሬ ሜትር |
4632/2009 |
ለድርጅት |
45,412,901.88 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ባህር ዳር ዲስትሪክት ቢሮ |
|
|
5 |
ጥሩ ኤ እርሻ ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
ካሳሁን እውነቴ አለልኝ |
በላይ ዘለቀ |
ጣና |
ባህርዳር |
- |
- |
6,000 ካሬ ሜትር |
ባህኢፖ/0062/09 |
ለኢንዱስትሪ |
62,133,310.57 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከ7፡00 እስከ 8፡00 ሰዓት |
አማራ ባንክ አ.ማ ባህር ዳር ዲስትሪክት ቢሮ |
|
ማሳሰቢያ፡-
1. ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4 ወይም ሃያ አምስት በመቶ (25%) በባንክ የተረጋገጠ የከፍያ ሰነድ (CPO) ብቻ በአማራ ባንክ አ.ማ ስም በማሠራት በማሰያዝ እና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
2. ከፍተኛ ዋጋ የሰጠው ተጫራች የጨረታው አሸናፊ ነው የሚባለው ከባንኩ አሸናፊነቱን የሚገልጽ ደብዳቤ በጽሑፍ ሲደርሰው ብቻ ነው።
3. የጨረታ አሸናፈው አሸናፈ መሆኑ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ ቀሪውን ገንዘብ አጠናቆ መከፈል ይኖርበታል፡፡ ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ሲፒኦ አይመለስለትም ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒአ በዕለቱ ይመለስላቸዋል፡፡
4. የሐራጁ አሸናፊ (ገዥ) ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግሥት የሚከፈሉ ከፍያዎችን የሊዝን ክፍያን ጨምሮ፣ ግብር፣ በዋጋው ላይ የሚታሰብ ተጨማሪ እሴት ታክስ (15%) ካለ ከስም ማዘዋወሪያ ጋር የተገናኙ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ታክስ እና ግብሮች ገዥው አሸናፈው/ ይከፍላል።
5. ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ (የቀበሌ፣ የመንጃ ፍቃድ፤ ፓስፖርት ወይም ብሄራዊ መታውቂያ) መያዝ ይገባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው አካላት ከሆኑ ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ግለሰብ ሥልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት የጸደቀ መመስረቻ ጽሑፍ (የመተዳደሪያ ደንብ)፤ ቃለጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት።
6. ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚለከተው መንግሥታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡
7. ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመነብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የጉብኝት ፕሮግራም ከወርካውትና ሪከቨሪ ከፍል ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በማስያዝ ጨረታው ከመካሄዱ ከ5 ቀን በፊት መጎብኘት ይችላል፡፡
8. ጨረታው በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓትና ቦታ ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ይካሄዳል፡፡ ነገር ግን ተበዳሪውም ሆነ መያዣ ሰጪው ባይገኙ ጨረታው በሌሉበት ይካሄዳል፡፡
9. ንብረቱን/ቶቹን በጨረታ አሸንፎ የገዛ ግለሰብ/ድርጅት የሽያጭ ገንዘቡን ከፍሎ ባጠናቀቀ በ15 ቀናት ጊዜ ውስጥ ንብረቱን መረከብ ያለበት ሲሆን በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ንብረቱን ካልተረክበ በንብረቱ ላይ ለሚደርስ ጉዳት ባንኩ ኃላፊነቱን አይወስድም፡፡ ገዥው በተጠቀሰው ጊዜ ንብረቶቹን ካልተረከበ ከንብረቶቹ ጋር በተያያዘ ለሚኖር ወጪ ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡
10. በባንኩ የብድር ፖሊሲ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ መሰረት የሚፈለገውን ማሰረጃ አሟልቶ ለቀረበ የጨረታ አሸናፈ ባንኩ ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡
11. ምዝገባ ከሐራጁ መዚያ ሰዓት 30 ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡
12. በወንድ አንቀጽ የተጠቀሰው ለሴት እና ሕጋዊ ሰውነት ላላቸው ድርጅትም ያገለግላል፡፡
13. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
14. ለበለጠ ማብራሪያ አማራ ባንክ አ.ማ 0115 58 27 64 ወይም ou 5 58 41 89 በሥራ ሰአት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
አማራ ባንክ አ.ማ
