ኦሮሚያ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውን በሰንጠረዡ ሳይ የተዘረዘሩትን ንብረቶች ባሉበት በግልጽ ሐራጅ ለወዳደር ለመሸጥ ይፈልጋል።
የሐራጅ ማስታወቂያ
ኦሮሚያ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውን በሰንጠረዡ ሳይ የተዘረዘሩትን ንብረቶች ባሉበት በግልጽ ሐራጅ ለወዳደር ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
ንብረት አስያዥ ስም |
ለጨረታ የቀረበው ንብረት ዓይነት |
አበዳሪው ቅርንጫፍ |
ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻና የቦታ ስፋት |
የጨረታ መነሻ ዋጋ |
የጨረታ ቀን፣ ሰዓት እና ጨረታው የሚካሄድበት ቦታ |
ጨረታው የወጣው |
||
|
ከተማ፣ ክ/ከ/ወረዳ/ቀበሌ |
የባለቤትነት ማረጋገጫ ቁጥር |
የቤቱ.ስፋት በካ.ሜ |
||||||||
|
1 |
ፒራሚድ ኮንስትራክሽን እና ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
ተበዳሪው |
የንግድ ህንጻ (G+2) |
አዲስ ከተማ |
ሐዋሳ ከተማ ምስራቅ ክ/ከተማ ቴሶ ቀበሌ |
20987 |
4,464 |
109,574,595.17 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከ4፡00-5፡00 ሰዓት ኦሮሚያ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ውስጥ |
ለመጀመሪያ ጊዜ |
|
2 |
ዋርካ ትሬዲንግ ሃውስ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር |
ተበዳሪው |
የኢንዱስትሪ ህንጻ (B+G+5) |
ወዴሳ |
ሸገር ከተማ፣ ገላን ክ/ከተማ፣ ሲዳ አዋሽ ወረዳ |
B/M/G/K/L/I/163/2002 |
16,166 |
604,056,780.70 |
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከ4፡00 – 5፡00 ሰዓት በዋና መስሪያ ቤት |
ለመጀመሪያ ጊዜ |
|
3 |
አቶ አብዲሳ መሀመድ ማሜ |
ተበዳሪው |
የመኖሪያ ቤት |
ቦስት |
አዳማ ከተማ፣ ቦሌ ክ/ከተማ፣ ጎሮ ቀበሌ |
OR001012014025 |
149.52 |
4,453,362.29 |
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከ 4፡00-5፡00 ሰዓት ኦሮሚያ ባንክ ቦስት ቅርንጫፍ ውስጥ (አዳማ ከተማ የሚገኝ) |
ለሶስተኛ ጊዜ |
1. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 25% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ/ሲ.ፒ.ኦ በኦሮሚያ ባንክ ስም አሰርተው ጨረታው በሚካሄድበት ዕለት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል። በጨረታው ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል::
2. ተ.ቁ 1 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ጨረታው በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ኦሮሚያ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ውስጥ ተ.ቁ 2 ቦሌ መንገድ ኦሎምፒያ አካባቢ አምራን ሆቴል አጠገብ የኦሮሚያ ባንክ ህግ አገልግሎት ቢሮ የሚገኝበት ናትሩት ሀውስ (ህንፃ) 9ኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ የጨረታ ክፍል ውስጥ እና ተ.ቁ 3 ኦሮሚያ ባንክ ሶስት ቅርንጫፍ ውስጥ ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ይካሄዳል:: ባለ ዕዳዎቹ ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል::
3. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐረጅ መዝጊያ ሰዓት 5 ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል:: የጨረታ መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ዋጋ የሰጠ ተጫራች ካልተለየ እስኪለይ ድረስ ጨረታው የሚቀጥል ይሆናል:: በጨረታው ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን ቦሚገልጽ ደብዳቤ ከባንኩ ህገ ለገሰገሱት ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል::
4. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረገ ይኖርበታል። በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ገቢ የማያደርግ የጨረታ አሸናፊ ያስያዘው ሲፒኦ ለባንኩ ገቢ ሆና ጨረታው ይሰረዛል:: በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚፈጠረው ልዩነት ይጠየቃል::
5. በባንኩ ብድር ፖሊሲ መሠረት የሚፈሰገውን ማስረጃ አሟልቶ ላቀረበ የጨረታ አሸናሬ ባንኩ ብድር ሊያመቻች ይችላል::
6. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራቾ ንብረቱን በማስተላለፍ ሂደት ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፤ ማናቸውም ግብር እና ታክስ፣ የሊዝ ክፍያ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የስም ማዘዋወሪያ እና ማንኛውም ከጨረታው ጋር በተገናኘ መንግስት የሚጠይቀው ክፍያ ይከፍላል። ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል::
7. ውዝፍ የሊዝ ክፍያን በተመለከተ ከእዳ ተመላሽ ብር ካለ ከተመላሽ ብር ላይ የሚከፈል ሲሆን ተመላሽ ብር ከሌለ ግን የንብረቱ ጨረታ አሸናሬ ውዝፍ የሊዝ ክፍያን ሙሉ በሙሉ የሚከፍል ይሆናል::
8. ተጫራቾች ሰጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዘው ለመጎብኘት ይችላሉ።
9. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 557 1372 እና ወይም 251911012049 ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት እና በ 011-273-42-93/011-273-43-04 ኦሮሚያ ባንክ አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ አንዲሁም በ 046-221-28 72 ኦሮሚያ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ፣ ለተ.ቁ 2 በ 011 111 8105 ኦሮሚያ ባንክ ወዴሳ ቅርንጫፍ እና ለተ.ቁ 3 በ 022-112-66-53 ኦሮሚያ ባንክ ቦስት ቅርንጫፍ ደወለው መጠየቅ ይቻላል::
10. ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ
