Tender Detail

Tender Details

  • Company Ethiopian Red Cross Society (የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር)
  • Address አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011 5 180175
  • Websitehttps://redcrosseth.org/blog/2022/07/29/19/
  • Deadline10 Jul 2026, 2:00 PM
  • magazineሪፖርተር
  • Bid Document Price400.00
  • opening date2026-07-10 14:30:00
  • Categories Food And Beverage , Cleaning And Janitorial Equipment , Stationery Materials

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የሰብአዊ አገልግሎቶች አቅም ግንባታ ማዕከል/ማሰልጠኛ ተቋም የምግብ ግብአቶችን፣ የጽሕፈት መሣሪያዎችን እና የጽዳት እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::


የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር

የሰብአዊ አገልግሎቶች አቅም ግንባታ ማዕከል/ማሰልጠኛ ተቋም

በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የሰብአዊ አገልግሎቶች አቅም ግንባታ ማዕከል/ማሰልጠኛ ተቋም የምግብ ግብአቶችን፤ የጽሕፈት መሣሪያዎችን እና የጽዳት እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

በዚሁ መሠረት ተጫራቾች፡-

1.     ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት እና ሌሎች መረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዶች ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፣

2.     በጨረታው ለመወዳደር ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ 2% በባንክ የተረጋገጠ ... አዘጋጅቶ ማስያዝ ይኖርበታል፣

3.     የጨረታ ሰነዱን በፖስታ አሽጎ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በግንባር ቀርቦ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከሰኞ እስከ አርብ ዘወትር በሥራ ሰዓት ሳሪስ አደይ አበባ ገባ ብሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የሰብአዊ አገልግሎቶች አቅም ግንባታ ማዕከል ማስገባት ይኖርባቸዋል፣

4.     ተጫራቾች ለጨረታው የተጋጀውን የምግብ ግአቶችን፣ የጽሕፈት መሣሪያዎችን እና የጽዳት እቃዎችን ዝርዝር መግለጫ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ይችላሉ፣

5.     የምግብ ግብአቶችን እና የጽዳት እቃዎችን አሸናፊው ተጫራች ለአንድ አመት ውል በመግባት ማቅረብ አለበት፤

6.     ጨረታው ሐምሌ 3 ቀን 2018 .. ከቀኑ 800 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከቀኑ 830 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፣

7.     ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች አለሟሟላት ከጨረታው ውጭ ያስደርጋል::

8.     ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

 

ለበለጠ መረጃ፡- 0114407460/011420235 ላይ መደወል ይቻላል

 

Save Tender