ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለገመጦ ጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ፕሮጀክት ጉድጓድ የማበልጸግ ፓምፕ ቴስት/ ስራ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ሀገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ ቁጥር 05/2018
ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለገመጦ ጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ፕሮጀክት ጉድጓድ የማበልጸግ ፓምፕ ቴስት/ ስራ በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቶች
1. በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው
2. ቫት የተመዘገቡ
3. በጨረታ ለመሣተፍ ከገቢዎች ፍቃድ ያላቸው
4. የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል
❖ የጨረታ ሰነደ የሚሸጥበት ጊዜና ቦታ፦
1. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይቀናት ድረስ የማይመለስ ብር 300.00/ሶስት መቶ ብር/ በሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሂሳብ ቁጥር 1000604259658 በኢትዮጲያ ንግድ ባንከ ገቢ በማድረግ የንግድ ፍቃዳቸውን ፎቶ ኮፒ ይዘው በመቅረብ ሲዳማ ኮንስትራከሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ሀዋሳ ከአዲሱ ገበያ ከፍ ብሎ ጊዮርጊስ ቤ/ከ አጠገብ ከሚገኘው ግዥና ንብረት አስተዳደርዳይሬክቶሬት ቢሮ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላሉ፡፡
❖ ጨረታው የሚከፈትበት እና ሰነዱ የሚቀርብበት ጊዜ፦
1. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን ከቀኑ ከ8:30 እስከ 11፡00 ሰዓት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ::
2. በማግስቱ በ12ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
3. ዕለቱ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን ይከፈታል::
❖ የጨረታ ዋስትና ፦
1. ማንኛውም ተጫራች 2% በባንክ የተረጋገጠ CPO ወይም ከስድስት ወር ያላነሰ ጊዜ ያለው በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ቢድቦንድ ዋስትና ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
❖ የጨረታ ሠነድ አስተሻሸግ ሁኔታ ፦
1. የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማስረጃ ፣ የልዩ እሴት ታከስ ተመዝጋቢነትና የታከስ ከፍያ ማረጋገጫ ሰነዶች ፣ በጨረታው ለመሳተፍ ከገቢዎች የተሰጠ ማስረጃ እና የጨረታ ማስከበሪያ በባንከ የተደገፈ CPO/ ከኦርጂናል የዋጋ ማቅረቢያ ጋር በአንድ ላይ በሰም ታሽገው መቅረብ አለባቸው፡፡ ፋይናንሻል ዶክመንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
2. ቴከኒካል ዶክመንት አርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ይህንን አስተሻሸግ ዘዴ ያልተጠቀመ ተጫራች ከጨረታው ይሠረዛል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0916071539/0911806709 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ሲኮስኮ)
