በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ለሚያስገነባቸው የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለጋሻ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለፁትን አቅርቦት እና ገጠማ ግዥዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር መሰፋ/ብ/ግ/ጨ/01/2018/19
በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ለሚያስገነባቸው የሠራዊቱ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለጋሻ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለፁትን አቅርቦት እና ገጠማ ግዥዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት1-passenger elevator /Lift/
ሎት2-supply and fix Roof water tanks
በዚህም መሠረት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው የምትሳተፉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
1. ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ VAT Registration Certeficate/ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተመዘገቡ እና የቲን ሰርተፊኬት የብቃት ሰርተፊኬት Tax clearance certificate የመንግስት የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው።
2. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብርብቻ) በመከፈል መ/ሰ/ፋ ግዥ ቡድን ክፍል ቢሮ ቁጥር 015 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማለትም ሎት (1) ብር 500,000 /አምስት መቶ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ በተመሰከረለት /ሲ.ፒ.አ/ በሁኔታላይ ያልተመሰረት ባንከ ጋራንቲ ብቻ በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ስም ከጨረታው ኦርጅናል ቴከኒካል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ሎት (2) ብር 250,000 /ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.አ/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት ባንክ ጋራንቲ ብቻ በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ስም ከጨረታው አርጅናል ቴከኒካል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
4. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ፋይናንሺያል እና ቴክኒካል ሰነዶቻቸውን ኦሪጂናል እና አንድ ኮፒ ለየብቻ ተለይቶ በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቢሮ ቁጥር 015 በመምጣት መሥሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። እንዲሁም ተያያዥ ዶክመንቶች ማቅረብ አለባቸው::
5. ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት አየር ላይውሎ በ16ኛው ቀን ልክ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ ከቀኑ 8፡30 መሰፋ ግዥ ቡድን ይከፈታል፡፡
6. የጨረታ አሸናፊዎች ማሸነፋቸው በጽሁፍ የሚገለጽላቸው እና የውል ስምምነት የሚፈፅሙ ይሆናል፡፡
7. በጨረታ ያላሸነፉ ድርጅቶች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል።
8. ፋውንዴሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0115572752
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ከሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስዳው ላንድ ማርከ ሆስፒታል አጠገብ
መከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን
