Tender Detail

Tender Details

  • Company የድሬዳዋ አስተዳደር የድል ጮራ ሆስፒታል
  • Address ድሬዳዋ , ኢትዮጵያ, Phone: 09-82-54-04-08
  • Website
  • Deadline19 Aug 2026, 10:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price1000.00
  • opening dateይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 የስራ ቀናት ከቆየ በኋላ በ16ኛው ቀን ጠዋት 4:00 ሠዓት
  • Categories Safety And Security , Security Service

በድሬዳዋ አስተዳደር የድልጮራ ሆስፒታል ለሆስፒታሉ ለ02(ሁለት አመት) የሚውል የጥበቃ አገልግሎት በግልፅ በጨረታ አወዳድሮ አገልግሎቱን ለመግዛት ህጋዊና ብቁ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


በድጋሚ የወጣ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ድ/ዳ/ድ/ጮ/ሆ/01/19

 

በድሬዳዋ አስተዳደር የድልጮራ ሆስፒታል ለሆስፒታሉ ለ02(ሁለት አመት) የሚውል የጥበቃ አገልግሎት በግልፅ በጨረታ አወዳድሮ አገልግሎቱን ለመግዛት ህጋዊና ብቁ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በዚሁ መሠረት በጨረታው ላይ ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች፣

1.    ተጫራቾች በዘርፉሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የ2019 ዓ/ም ግብር የከፈሉ፣ በተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

2.    በመንግስት ግዢ አቅራቢ የተመዘገቡና የተመዘገቡብትን ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እና ከፌደራል ፖሊስ የታደሠ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ።

3.    ተጫራቾች የታክስ መለያ ቁጥር (TIN No.) ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።

4.    ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 1000.00(አንድ ሺ ብር) በመክፈል በድል ጮራ ሆስፒታል ቢሮ ቁጥር A/02 በመቅረብ ሠነዱን መግዛት ይችላሉ።

5.    መስፈርቱን የሚያሟላ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 20,000.00 (ሀያ ሺህ ብር) በባንክ በተመስከረለት ቼክ ወይም(CPO) ከጨረታው ኦርጅናል ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።

6.    ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ መቀበያ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

7.    የጨረታ ሰነዱ የሚከፈትበት ቀን ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 የስራ ቀናት ከቆየ በኋላ በ16ኛው ቀን ጠዋት 4:00 ሠዓት ተዘግቶ ከቀኑ 4:30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታለግዢ ፋ/ን/አስ/ዳይሮክትሬ ቢሮ ቁጥር A/02 ይከፈታል።

8.    የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ እንደተገለፀለት አስፈላጊውን የጨረታ ውል ማስከበሪያ በማስያዝ ከሆስፒታሉ ጋር ውል መፈራረም አለበት:: ይህ ባይፈፀም የጨረታ አሸናፊነቱን በመሰረዝ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ይሆናል።

9.    ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን፤ ሙሉ አድራሻቸውን እና ፊርማቸውን እንዲሁም የተሟላ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።

10.        ከግል ስራና አገናኝ ኤጀንስ በአገር ውስጥ ስራና ሠራተኛ የማገናኘት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ።

11.        ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።

 

አድራሻ:- በድሬዳዋ አስተዳደር የድል ጮራ ሆስፒታል

ስልክ ቁጥር፡- 025-211-5692 / 0982 540 408 / 0901 103 211 ፤ ፖስታ ሳጥን ቁጥር 177

 

የድል ጮራ ሆስፒታል

✨ messages.ai_summary
- Open tender for a two-year security guard service for Dil Chora Hospital, Dire Dawa, issued by the Dire Dawa Administration Dil Chora Hospital (Tender No. ድ/ዳ/ድ/ጮ/ሆ/01/19). - Bid documents can be purchased for a non-refundable 1,000 ETB for 15 consecutive working days from newspaper publication; bids close on the 16th day at 4:00 AM and are opened at 4:30 AM at the hospital’s procurement office A/02. - A bid bond of 20,000 ETB must be submitted as a certified bank cheque or CPO with the original bid document. - Bidders must have a valid sector business license, paid 2019 E.C. tax, VAT registration, TIN, government procurement supplier registration, a renewed Federal Police license, and a private employment agency license.
Save Tender

የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ለ2019 በጀት ዓመት፡- CCTV CAMERA በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

READ MORE
አቃቂ ቤዚክ ሜታልስ ኢንዱስትሪ በጥበቃ አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ ዓመት ማሰራት ይፈልጋል፡፡

READ MORE