የአድዋ ድል መታሰቢያ ለ2019 በጀት አመት የሚያስፈልጉትን የጥበቃ እና የገፀ-ምድር ስፍራዎች ማስዋብ አገልግሎቶች በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር ፡- አ/ድ/መ/-002/2019
የአድዋ ድል መታሰቢያ ለ2019 በጀት አመት የሚያስፈልጉትን የጥበቃ እና የገፀ-ምድር ስፍራዎች ማስዋብ አገልግሎቶች በብሔራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ ፈቃደኛ የሆናችሁ ተጫራቾች እንድትሳታፉ እያጋበዝን የአገልግሎቶቹ ዝርዝር ሁኔታ ከታች ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል።
|
ምድብ ቁጥር
|
የሚገዛው አገልግሎት አይነት
|
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) ብር
|
|
ሎት 1
|
የጥበቃ አገልግሎት ግዥ
|
100,000 ብር
|
|
ሎት 2
|
የገፀ-ምድር ማስዋብ አገልግሎት ግዥ
|
50,000 ብር
|
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
1. በአቅራቢነት የተመዘገቡ፣ በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ።
3. ተጨማሪ እሴት ታከስ /VAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
4. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500/አምስት መቶ ብር/ በአድዋ ድል መታሰቢያ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000613546867 በመክፈል ደረሰኝ /ስሊፕ/ ይዞ በመቅረብ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 /አስር/ ተከታታይ ቀናት ቅደሜን ጨምሮ ይሆናል።
5. ጨረታው በ10ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡30 ላይ L2 መሰብሰቢያ ክፍል ቢሮ ቁጥር 214 ይከፈታል።
6. ተጫራቾች ሌሎች መረጃዎችን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናውቃለን።
7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
8. የጨረታ ሰነዱ ፒያሳ አራዳ ህንጻ ፊት ለፊት አድዋ ድል መታሰቢያ አስተዳደር ቢሮ ሌቭል - 2 ግዥ ክፍል ይገኛል።
9. ተጫራቾች የቴክኒክ እና የፋይናንስ ሰነዳቸውን በተለያየ ፖስታ አሽገው አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
አድራሻ፡-ፒያሳ አራዳ ህንጻ ፊት ለፊት የአድዋ ድል መታሰቢያ ፋይናንስና አስተዳደር ዳ/ዳይሬክተር
ስልክ ቁጥር: +251 93 060 0429 / +251 91 961 2935
የአድዋ ድል መታሰቢያ
