ተደራሽ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/የህብረት ስራ ማህበር ለመስሪያ ቤቱ ስራ አገልግሎት የሚውሉ ቋሚ የኤሌከትሮኒከስ እቃዎች ፕሪንተር፣ ላፕቶፕ እና ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር በአስቸኳይ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፈዎች ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
አስቸኳይ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ተደራሽ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/የህብረት ስራ ማህበር ለመስሪያ ቤቱ ስራ አገልግሎት የሚውሉ ቋሚ የኤሌከትሮኒከስ እቃዎች ፕሪንተር፣ ላፕቶፕ እና ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር በአስቸኳይ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፈዎች ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት1. ቋሚ ዕቃዎች
በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይፈልጋል፡፡
1. አግባብነት ያለ ሕጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣
2. አገባብነት ያለው ሕጋዊ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት
3. የተጨማሪ እሴት ታከስ፣
4. የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት፤
5. ግብር የከፈሉና እንዲሁም በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ወይም አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ በዕቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ለመመዝገባቸው የምስከርወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤ ቫት ተመዝጋቢና ቲን ነምበር ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው:: ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ቅዳሜን ጨምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በህብረት ሥራ ማህበሩ ዋና ቢሮ በመገኘት ለሙሉ ሰነድ 500 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መወሰድ ይችላሉ፣
6. ተጫራቾች እያንዳንዱን ዕቃ የሚሸጡበትን ዋጋ ከነቫቱ በመግለጽ ፊርማ ማህተም እና አድራሻቸውን በመጥቀስ በታሸገ ፖስታ ዋናውን እና ኮፒውን በ2 ፖስታ በማድረግ ሙሉ አድራሻቸውንና የጨረታውን አይነት በመጥቀስ በህብረት ሥራ ማህበሩ ዋና ቢሮ ፋይናንስ ከፍል ገቢ ማድረግ አለባቸው
7. ተጫራቾች የተጠቀሱትን ዕቃዎች በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡
8. ጨረታው በማስታወቂያ በወጣ በ6ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጐ በ6ኛው የስራ ቀን 4፡ 30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቢሮው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
1. 9, አንድ ተጫራች ሌላው በሰጠው ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም፡፡ ማህበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
9. በጨረታ ለቀረቡት እቃዎች ናሙና የሚቀርብባቸው እቃዎች የማወዳደሪያ ሰነዱ ላይ በተገለፀው እስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው፡፡ ይህ ሆኖ ካልተገኝ ተጫራቹ ከጨረታው ውጪ ይደረጋል፡፡
10. የውል ማስከበሪያ 10% ከጠቅላላ ዋጋው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
11. ለጥቃቅንና አነስተኞች የግዥ መመሪያ በሚፈቅደው መሰረት ልዩ አስተያየት ይደረገላቸዋል፡፡
2. አድራሻ – አራት ኪሎ አሮጌው ፖስታ ቤት 1ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር 7078
ተደራሽ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/የህብረት ሥራ ማህበር
