Tender Detail

Tender Details

  • Company የቦሌ ወረገኑ ቅደመ አንደኛ፣ አንደኛ እና የመጀ/ደ/ት/ቤት
  • Address ከጎሮ አደባባይ ወደ ቱሉ ዲምቱ የሚወስድ መንገድ ወደ ቀኝ 2 ኪሎ ሜትር ላይ : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0118669955
  • Website
  • Deadline22 Aug 2026, 5:30 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Priceብር/200.00/ ሁለት መቶ ብር
  • opening dateበቀጣይ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተጠቀሰው 4፡00 ሰዓት
  • Categories Other , Services , Construction Works

የግልፅ ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ


የግልፅ ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ

1ኛ ዙር መለያ ቁጥር 001/2018

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ወረገኑ ቅደመ አንደኛ፤ አንደኛ እና መካከለኛ ደ/ት/ቤት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ሎት ዝርዝር ይሆናሉ፡፡

ተ.ቁየሎት ዝርዝርየጨረታ ማስከበሪያ በኢትዮ ብር
1የደንብ ልብስ20,000
2የስፖርት ትጥቅ20,000
3አላቂ የቢሮ ዕቃዎች40,000
4አላቂ የፅዳት ዕቃዎች40,000
5የሕንፃ ቁሳቁስ መግዣ60,000
6የኤሌክትሮኒከስ መግዣ65,000
7የትምህርት ዕቃዎች30,000
8የሕክምና ዕቃዎች10,000
9ሕትመት10,000
10ልዩ ልዩ መሣሪያዎች10,000
11የኤሌክትሮኒከስ ጥገና10,000
12የሕንፃ ቁሳቁስ ጥገና10,000
13የጭነት አገልግሎት10,000
14የትራንስፖርት አገልግሎት10,000
15ምንስትርምንግ /ልዩ ልዩ10,000

* ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳዲሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት ጨረታውን ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሕጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መሆን አለባቸው፡፡

  1. ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበት ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር መከፈላቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. በገንዘብና በኢኮኖሚ ልማት ሚንስቴር በአቅራቢነት የተመዘገበና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
  3. የ2019 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያለው፡፡
  4. ተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
  5. የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በየሎቱ የማይመለስ ብር/200.00/ ሁለት መቶ ብር በመከፈል የተዘጋጀውን ሰነድ ከተቋሙ ቢሮ ቁጥር (3) እየቀረቡ መግዛት ይቻላል፡፡
  6. ተጫራቶች ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10/አስር (ተከታታይ የሥራ ቀናት ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር (3) ድረስ በመምጣት ዋጋው የተሞላበት የጨረታውን ሰነድ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን ለየብቻው በማሸግ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸዉ::
  7. የጨረታው ሳጥን በ10ኛው ቀን 11:30 ላይ ይታሸጋል፡፡ በቀጣይ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተጠቀሰው 4፡00 ሰዓት ተጫራች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከላይ የተጠቀሰውን ብር ከባንክ በተረጋገጠ /CPO) ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለሚወዳደሩበት ናሙና ለሚቀርብባቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው የማይቀረብባቸው ቋሚ ዕቃዎች መሥሪያ ቤቱ ባቀረበው እስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው::
  10. የጨረታ አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈውን ዕቃ 10% ከባንክ የተረጋገጠ /CPO/ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
  11. የጨረታ አሸናፊ ድርጅት ያሸነፈውን ዕቃ በራሱ ትራንስፖርት ቦሌ ወረገኑ ቅደመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደ/ት/ቤት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  12. መ/ቤቱ ለጨረታ ከቀረበው ዕቃ እስከ 20% የመቀነስም ሆነ የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው::
  13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፍል ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

አድራሻ ስልክ ቁጥር 0118669955/0924264427 ከጎሮ አደባባይ ወደ ኮዬ ፈጬ የሚወስድ መንገድ ወደ ቀኝ 3 ከሎ ሜትር ላይ ይገኛል፡፡

ቦሌ ወረገኑ ቅደመ አንደኛ፤ አንደኛ እና መካከለኛ ደ/ት/ቤት

✨ messages.ai_summary
Open tender for supplying goods and services to Bole Weregenu Primary and Middle School, including uniforms, sports gear, office/cleaning supplies, building materials, electronics, medical items, printing, maintenance, and transport. Bidders need valid licenses, tax clearance, and supplier registration.
Save Tender