የተለያዩ ዕቃዎች (የግንባታ እቃዎች፣ የኤሌክትሮኒከስ፣ የፈርኒቸር፣ ያገለገሉ ጎማዎች፣ የውሃ እቃዎች፣ ቦንዳዎች እና ሌሎችም) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ
ዕቃዎችን ስመሸጥ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ ሠመራ/ስተአ/003/2018
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ሰመራ ቅ/ፅ/ቤት በሚገኘው ቅጥር ግቢ እና መጋዝን የሚገኙትን የተለያዩ ዕቃዎች (የግንባታ እቃዎች ፣ የኤሌክትሮኒከስ፣ የፈርኒቸር ፣ ያገለገሉ ጎማዎች፣ የውሃ እቃዎች፣ ቦንዳዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የቅ/ፅ/ቤቱ ባወጣው የዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ መወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች:-
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የሽያጭ ጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/ በመከፈል ሰመራ በሚገኘው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ቅ/ፅ/ቤት ቅጥር ግቢ ፋይናንስ ቢሮ በመገኘት እና ክፍያ በመፈጸም ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከነሐሴ 05/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6.30 ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል፡፡
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% ለስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ሰመራ/ቅ/ፅ/ቤት/ Refugees and Returnees Service /በሚል የተዘጋጀ የከፍያ ማዘዣ /CPO/ የባንክ ዋስትና /Bank Gurantee/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራጭ ከነሐሰ 05/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ሰመራ በሚገኘው ቅ/ፅ/ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ዕቃዎቹን መመልከት ይችላል። ቅዳሜና እሁድ የስራ ቀናት አይደሉም።
- ጨረታው ሰመራ በሚገኘው የቅ/ፅ/ ቤት ቅጥር ግቢ የሚካሄድ ሲሆን የጨረታው ሳጥን ነሐሴ 14 ከቀኑ 5፡30 ታሽጎ በዕለቱ ከቀኑ 9፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊ ተጫራቶች ለጨረታው ያሰያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቶች ያሰያዙት የጨረታ ዋሰትና በ3 ቀናት ውሰጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- ተጨራቶች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ወይም በማስታወቂያ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃዎችን መረከብ አለባቸው::
- በተራ ቁጥር 6 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ከፍያውን ገቢ ያላደረገ ተጨራች ለጨረታው ማስከበርያ ያስያዘው ሲፒኦ ለቅፅ/ ቤቱ ገቢ በማድረግ የተሻለውን አማራጭ የመውሰድ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ቅ/ፅ/ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251923966445 ወይም 251966016656 ደውሎ መጠየቅ ይችላል፡፡
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ሰመራ ቅ/ፅ/ቤት
✨ messages.ai_summary
Open tender for the sale of various items (construction materials, electronics, furniture, used tires, water equipment, bonds, and others) as-is, by the Refugees and Returnees Service, Semera Branch Office. Bidders must purchase tender documents and provide a 2% bid security.
