Tender Detail

Tender Details

  • Company Amhara Bank S.C
  • Address , Phone: 251115582905
  • Website
  • Deadline04 Sep 2026, 2:00 AM
  • magazineReporter Tenders
  • Bid Document Price
  • opening date2026-09-04 02:30:00
  • Categories Event Organizing And Planning

አማራ ባንክ አ.ማ የ2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ለሚያካሄደው የባለአክስዮኖች ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሁነት ዝግጅት አገልግሎት የሚያቀርቡ ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡


አማራ ባንክ .

Amhara Bank S.C.

ሀገር አቀፍ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የሁነት አገልግሎት ግዥ

የጨረታ ቁጥር፡- አባ/ግፋማመ/ሀግጨ/029/2026

  • አማራ ባንክ አ.ማ የ2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ለሚያካሄደው የባለአክስዮኖች ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሁነት ዝግጅት አገልግሎት የሚያቀርቡ ድርጅቶችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ተ.ቁ
የአገልግሎት ዓይነት
ጨረታው የሚዘጋበት ቀንና ሰዓት
ጨረታው የሚከፈትበት ቀንና ሰዓት
የጨረታ ማስከበሪያ
1.
የሁነት ዝግጅት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት (Event Organizing Service)
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ 8፡00
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡30 ሰዓት
300,000.00

 

  • ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ከለገሃር ወደ አዲስ አበባ ስታዲየም በሚወስደው መንገድ መብራቱን እንደተሻገሩ የአመልድ ህንፃ ላይ በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ግዥና ፋሲሊቲዎች አስተዳደር መምሪያ 20ኛ ፎቅ ላይ ከነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ) የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች ከጨረታው በኋላ የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) ከላይ በተገለፀው መሠረት ከጨረታው መክፈቻ ቀን ጀምሮ ለ120 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ሲፒኦ ወይም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በሚሰጥ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) በአማራ ባንክ አ.ማ. ስም አሰርተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ተጫራቾች የሙያ ፈቃድ፣የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ታክስ ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  • ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ከላይ በተገለፀው ቀን እና ሰዓት መሠረት ማስገባት አለባቸው፡፡ ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በኋላ የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡
  • የጨረታው ሰነድ አማራ ባንክ አ.ማ. 20ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የግዥና ንብረት አስተዳደር መምሪያ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት መግባት ይኖርበታል፡፡
  • ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት አማራ ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ግዥና ፋሊቲስ መምሪያ 20ኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡
  • ከላይ የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎች አለማሟላት ከጨረታው ውጭ (ውድቅ) ያስደርጋል።
  • ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011558-29-05 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
  • ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
Save Tender