ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት በመጪው ዓመት በከፍተኛ ድምቀት የሚዘጋጀውን “የ2019 ዓ.ም የገና እና የፋሲካ ዋዜማ ኤግዚቢሽን፣ባዛርና ፌስቲቫል” ለማዘጋጀት የሚያስችል በሰነዱ ላይ የተጠቀሰውን ህጋዊና አግባብነት ያለው ፍቃድ ያላቸውን አዘጋጆች (Event Organizers) በግልፅ ጨረታ በማወዳደር እንዲያዘጋጁ ይጋብዛል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት በመጪው ዓመት በከፍተኛ ድምቀት የሚዘጋጀውን “የ2019 ዓ.ም የገና እና የፋሲካ ዋዜማ ኤግዚቢሽን፣ባዛርና ፌስቲቫል” ለማዘጋጀት የሚያስችል በሰነዱ ላይ የተጠቀሰውን ህጋዊና አግባብነት ያለው ፍቃድ ያላቸውን አዘጋጆች (Event Organizers) በግልፅ ጨረታ በማወዳደር እንዲያዘጋጁ ይጋብዛል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ሙሉ መረጃ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ከነሐሴ 24/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት 7 ተከታታይ ቀናት መስቀል አደባባይ በሚገኘው ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ) በመክፈል መግዛት /መውሰድ/ ይችላሉ፡፡
የጨረታ ሰነዱን ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 እስከ 8፡25 ድረስ ማስገባት የሚቻል ሲሆን የጨረታ ሳጥኑ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት በዚሁ ዕለት ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት በማዕከሉ የመሠብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
ለበለጠ መረጃ +251 515 2657/+251 911 665 843
ማዕከሉ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ ህጋዊ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
