የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ክራይ አገልግሎት ግዥ
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ማ/ኢ/መ/ባ/ማሽ/001/19
መ/ቤታችን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በስሩ ባሉ ዲስትሪክቶችና አከባቢያቸው የመንገድ ፕሮጀከቶች አገልግሎት የሚውል የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ማለትም ዶዘር፣ግሬደር፣ ኤክስካቫተር፣ሮለር፣ሎንግ ቤዝ መኪና እና ፒክ አፕ መኪና ክራይ አገልግሎት ግዥ ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።
በመሆኑም፡-
1. 1.ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የዘመኑን ግብር የተከፈለበትን ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደ የንግድ ሥራ ወይም አገልግሎት ሥራ ፈቃድ፣የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት፣ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ መሳተፍ የሚያስችል የምስክር ወረቀት፣የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች የፋይናንሻል ፕሮፖዛል አንድ ዋና እና ኮፒ እንዲሁም ቴክኒካል ፕሮፖዛሉን አንድ ዋና እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማድረግ ኦሪጂናል እና ኮፒ በማለት እና የጨረታ ማስከበርያውን በተለየ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ) ብቻ በመከፈል በባለሥልጣኑ ዋና መ/ ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም ቢሮ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
4. የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሰረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው።
5. አቅራቢዎች ጨረታውን ገቢ የሚያደርጉት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ይሆናል። ጨረታው በዚያው ቀን ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሣሣይ ሠዓት ይሆናል።
6. ተጫራቾች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ካላቸው የፋይናንስ ተቋም በቅድመ-ሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ሲፒኦ (CPO) ለእያንዳንዱ ማሽን ብር 10,000.00(አስር ሺህ) ብቻ ሲሆን ለሎንግ ቤዝ መኪና እና ፒክ አፕ መኪና ለእያንዳንዳቸው ብር 50,000(ሀምሣ ሺህ) በማሰራት ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በኢንሹራንስ ዋስትና የሚቀርብ የጨረታ ማስከበርያ ተቀባይነት የለውም።
7. ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሰረት ጨረታውን ማቅረብ አለባቸው። ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጪ የሚቀርብ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
8. መ/ቤቱ የተሸለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9. ለበለጠ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም
ስልክ ቁጥር፡- 011 365 9932
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን
