Tender Detail

Tender Details


በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በእንስሳት እና አሣ ሀብት ልማት ቢሮ በክልሉ በጦርነት የተጐዱ አካባቢዎች የእንስሳት መሰረተ ልማቶችን መልሶ ማቋቋም ፕሮጀክት ለፕሮጀክቱ አገልግሎት የሚውል በ2018 ዓ.ም በሪስቶር ፕሮጀክት በጀት የሞተር ሳይክል እና የመኪና ጎማ በሀገር ውስጥ ገበያ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ET-AMH-RESTORE-GO-REQ-032/2018

 

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በእንስሳት እና አሣ ሀብት ልማት ቢሮ በከልል በጦርነት የተጐዱ አካባቢዎች የእንስሳት መሰረተ ልማቶችን መልሶ ማቋቋም ፕሮጀክት ለፕሮጀክቱ አገልግሎት የሚውል በ2018 ዓ.ም በሪስቶር ፕሮጀክት በጀት የሞተር ሳይክል እና የመኪና ጎማ በሀገር ውስጥ ገበያ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

1.      በዚህ የንግድ ዘርፍ /ዘርፎች/ የሥራ ፈቃድ ያለው፣ የዘመኑን ግብር ለመከፈሉና በገንዘብ ሚ/ር/ቢሮ ጽ/ቤት የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት (TIN) ማስረጃ ማቅረብ የሚችል በባህር ዳር ከተማ እንስሳት እና አሣ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 04 በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /መቶ ብር/ በመግዛት የሚወዳደሩበትን ሰነድ በእያንዳንዱ ሎት የቴከኒክ የዋጋ ብሎ በመለየት በሁለት ኮፒ ተሰርቶ በደንብ በማሸግ የጨረታውን ዓይነት፣የሎት ቁጥርና የጨረታ ቁጥር በፖስታ ላይ እንዲፃፍ ሆኖ ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል።

2.    ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ ብር 1% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ይህ ሳይሆን ቢቀር ወይም ከ1% ቢያንስ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተጫራቹ ከውድድር ውጭ ይሆናል።

3.    ተጫራቾች የሚሣተፉበት የጨረታ ዓይነትና ሎት በተሸጠላቸው የጨረታ ሰነድ መሰረት የዋጋ ማቅረቢያ እና የቴከኒክ ብሎ በመለየት በተለያየ ፖስታ በኦርጂናል እና ኮፒ ዶከመንት ለይተው ፖስታውን ማሸግና ማቅረብ አለባቸው።

4.    ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት የአሸነፈውን እቃ 30 /ሰላሳ/ ቀን ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለበት።

5.    ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት የተሸጠለትን የጨረታ ሠነድ በአግባቡ አንብቦ በትክከል በተሠጠው የጨረታ መመሪያ መሠረት የመሙላት ግዴታ አለበት፡፡ ከተሰጠ መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ሠነድ ተቀባይነት የለውም።

6.    ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 /አስራ አምስት/ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በተዘጋ በዚያው የሥራ ቀን በ4፡30 በጽ/ቤቱ ይከፈታል ይሁን እንጂ 16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን 4፡30 ላይ እንዲከፈት ይደረጋል።

7.    ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 18 76 37 33 ወይም 09 18 48 95 96 ጠይቆ መረዳት ይቻላል።

8.    ፕሮጀክቱ ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ በተናጠልም ሆነ በጥቅል ዕቃዎችን በመምረጥ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው።

9.    ፕሮጀክቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ጨረታውን የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በእንስሳት እና አሣ ሀ/ል/ቢሮ ሪስቶር ፕሮጀክት/ባህር ዳር/

✨ messages.ai_summary
Procurement of motorcycle and vehicle tires for the Amhara National Regional State's Livestock and Fish Resource Development Bureau, under the RESTORE project, to rehabilitate livestock infrastructure in war-affected areas. Bidders must hold a valid trade license, current tax clearance, and TIN certificate.
Save Tender