በባሌ ዞን የሮቤ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒከስ፣ ፕላስቲከ ቧንቧዎች (Roll Pipe) ፕላስቲክ መገጣጠሚያዎች፣ Gl መገጣጠሚያዎች፣ ሞተር ሳይክል እና የሞተር ሳይክል እቃዎች Calcium Hypho chloride(ካሎሪን) ፣ የመኪና ጎማዎችና መለዋወጫ እንዲሁም የሰራተኛ የደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግዢ ጨረታ ማስታወቂያ
በባሌ ዞን የሮቤ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የተለያዩ የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት እቃዎች፣ ኤሌክትሮኒከስ፣ ፕላስቲከ ቧንቧዎች (Roll Pipe) ፕላስቲክ መገጣጠሚያዎች፣ Gl መገጣጠሚያዎች፣ ሞተር ሳይክል እና የሞተር ሳይክል እቃዎች Calcium Hypho chloride(ካሎሪን) ፣ የመኪና ጎማዎችና መለዋወጫ እንዲሁም የሰራተኛ የደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተለውን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳዳሩ ይጋብዛል፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል በተሰማራበት ዘርፍ ህጋዊና የዘመኑን ግብር የከፈለበት የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በመክፈል ከሮቤ ከተማ መጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ቢሮ ቁጥር 11 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋና እና ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በማስታወቂያ ከወጣበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወከሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ እለቱ በአል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣይ የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ 2% ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በጨረታው ሰነድ በተጠቀሰው መሰረት በግልጽ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በሙሉ የመጫኛና የማጓጓዣ ወጪውን በመቻል መስሪያ ቤቱ ንብረት ክፍል ድረስ በማምጣት ገቢ ማድረግ አለባቸው፡፡
- የእቃዎቹን ዋጋ መስሪያ ቤቱ የሚከፍለው ተጫራቹ ለማቅረብ ውል የፈረመባቸውን እቃዎች ሙሉ በሙሉ በንብረት ክፍላችን ገቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ሲቀርብ ነው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ማሸነፋቸው በደብዳቤ በተገለፀላቸው በ3 ቀን ውስጥ መ/ቤት ቀርበው ውል መፈራረም አለባቸው፡፡
- ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0966696974/ 0904449498 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የሮቤ ከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት
