በማ/ኢ/ክ/የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለዞኑ ሴክተር መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሞተር ሳይክሎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በማ/ኢ/ክ/የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለዞኑ ሴክተር መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሞተር ሳይክሎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፤
- የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ፤
- በተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት የሚያቀርቡ፤
- የጨረታ ዋስትና 20,000 (ሃያ ሺህ ) ብር ማስያዝ የሚችሉ፤
- የጨረታ ሳጥኑ ጨረታው ከወጣ ከ7ኛው ቀን በኋላ ባለው የስራ ቀን 8፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ:-
- ተጫራቾች ያስያዙት ዋስትና አንሶ ከተገኘ ከጨረታው ይሰረዛል።
- የተወዳዳሪዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታ መክፈቻ ቀኑን አይለውጠውም።
- መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- 0467710586
ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የስልጤ
ዞን ፋይናንስ መምሪያ
