በማ/ኢ/ክ/መንግስት በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት ለ2017 በጀት አመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ለቢሮ እና ሆስፒታል ግንባታዎች እና የአገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል
የጨረታ ማስታወቂያ
በማ/ኢ/ክ/መንግስት በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት ለ2017 በጀት አመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ለቢሮ እና ሆስፒታል ግንባታዎች እና የአገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል የግንባታው አይነቶች ።
1. የፍርድ ቤት ቢሮ ግንባታ
2. የት/ቤት ብሎክ ግንባታ የእጅ
3. የሆስፒታል ብሎክ ግንባታ የእጅ
በመሆኑም ተጫራች ድርጅቶች
- በተሰማሩበት ዘርፍ ህጋዊና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢና ቲን ነምበር ፤የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፤ የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች በጽ/ቤቱ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 300/ሶስት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ድረስ የአ/ው/ወ/ፋ/ ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በመምጣት ሰነዱን መግዛት ትችላላችሁ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ዋስትና 25,000 /ሀያ አምስት ሺ ብር/ ብቻ በሁኔታዎች ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ ወይንም በሲፒኦ በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም በማሰራት በታሸገ ፖስታ የፋይናንሺያል እና ቴከኒካል የጨረታ ሰነድ ማስገባት አለባችሁ፡፡
- የግንባታ ማጠናቀቅያ ግዜ የውል ስምምነት ከተፈጸመ ቀን ጀምሮ በ90 ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡
- የጨረታ ዋጋ ጸንቶ የሚቆይበት ግዜ ጨረታው ከተከፈተ እለት ጀምሮ 90 ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡
- አሸናፊ ተጫራች የውሉን አስር ፐርሰንት /10/ ውል አፈጸጸም ዋስትና ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ሀያ ፐርሰንት የቅድመ ክፍያ ሲጠይቅ ተመጣጣኝ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ ያለ ክፍያዎች ሲጠይቅ ብቻ የሚከፈለው ይሆናል፡፡
- የተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ የሆስፒታሉ 04 /አራት/ ብሎክ ሲሆን አንድ ተወዳዳሪ መጫረት የሚችለው 04 /አራት/ አንድ ተጫራች ማሸነፍ የሚችለው 01 /አንድ/ ብሎክ ብቻ ነው፡፡
- ወረዳው ላይ የሚሰሩ ተጫራቾች አሁን ላይ በወረዳው ውስጥ የሚሰሩ ስራዎች ሰባ አምስት ፐርሰንት በላይ የደረሱ መሆን አለባቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ማንኛውም ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ለእያንዳንዱ የማይመለስ 300 ብር በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከአ/ዉ/ወ/ፋ/6/ ቤት ቢሮ ቁጥር 10 በመውሰድና በመሙላት መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን። በመሆኑም ጨረታው የሚከፈተው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከ15ኛው ቀን በኋላ ባለው የስራ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት /ባልተገኙበት/ከቀኑ በ6፡00 ሰአት ታሽጎ ከቀኑ በ8፡00 ሰአት በቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል
በተጨማሪም ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሰነድ ቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ፡ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ 0968473512 ወይም 0917010309
የአስቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት
