የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከዚህ በታች በሎት የተገለፁትን በጨረታ መግዛት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 04/2017
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከዚህ በታች በሎት የተገለፁትን በጨረታ መግዛት ይፈልጋል።
የግዥው አይነት
ሎት 1 የሆቴል አገልግሎት ግዥ
ሎት 2 የተለያዩ የመኪና ጎማዎች ግዥ
- በዘርፍ ህጋዊ ፍቃድ ያለውና የ 2016 የታደሰ የንግድ የስራ ፍቃድ ያላቸው::
- ለእቃ አቅራቢነት ስለመመዝገባቸው እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 50.000 /ሃምሳ ሺ ብር/ ወይም በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ስም CPO /ጋራንትድ/ ቦንድ/ በማሰራት ማስያዝ የሚችሉ
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከመጨረሻው ቀን በኋላ ለተጨማሪ 28 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን የአንዱ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስን ያካተተ ዋጋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ቢሮው በሰጣችሁ ፎርማት ላይ በመሙላት እና የድርጅታችሁን ማህተም ፊርማና ሙሉ አድራሻችሁን በመግለጽ
- ፋይናንሽያል አንድ ኦርጅናል እና ፋይናንሽያል አንድ ኮፒ
- ቴክኒካል አንድ ኦርጅናል እና ቴክኒካል አንድ ኮፒ በማድረና በሰም በታሸገ በተለያዩ ፖስታዎች ማቅረት ይኖርባችኋል፡፡
- ለሎት 2 ቢሮው በሚያቀርበው ዝርዝር /ናሙና/ መሰረት ማቅረብ የሚችል
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከሰኞ - ዓርብ ከ 2፡30 -11:00 ሰዓት ድረስ የግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 803 በዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ በ11ኛው ቀን ማለትም የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ተጫራቾች ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት /ማቅረብ / አይቻልም፡፡
- ቢሮው ብዛቱን በተመለከተ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት መቀነስና መጨመር የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118126179/011703024/ በመደወል መረጃ መጠየቅ ይቻላል
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ውቤ በረሃ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 803
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ
