የአልጋ ኪራይ እና የምግብ መስተንግዶ አገልግሎት ጨረታ
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ በ2019 ዓ/ም ለክለቡ ስፖርተኞች በአንድ ሆቴል ውስጥ የሆነ የአልጋ ኪራይ እና የምግብ መስተንግዶ በጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት፤-
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አቅራቢዎች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በሥራ መስኩ ሕጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆነ
- የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለተመዘገቡ ጨረታዎች የጨረታ ማስከበሪያ 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ/ ብር በባንክ የተረጋገጠ (የምስክር) ሲፒኦ (CPO) ወይም ቢድ ቦንድ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ቢሮ በመቅረብ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 /ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናትን በመጠቀም ብር 3,000.00 /ሶስት ሺህ/ በመከፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የተወዳዳሪ ሆቴል ደረጃ በባሕልና ቱሪዝም ሰርተፍኬት የተሰጠው ከባለ 3 ኮኮብ በላይ የሆነ መሆን አለበት ማስረጃውንም አያይዞ ኮፒ ማቅረብ አለበት፡፡
- የጨረታ ሠነዱ በሰም ለየብቻቸው በታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ፋይናንሻል በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ቀናትን በመጠቀም በሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ፋይናንስ ቢሮ አርተፍሻል ሜዳ ቢሮ ቁጥር 1 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት 4፡00 ሰዓት በቢሮ ቁጥር 1 ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን ቅዳሜ /እሁድ/ ከሆነ እንዲሁም የበዓላት ቀን ከሆነ በተመሣሣይ ሰዓት በሚቀጥለው የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ ተጠብቆ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር፡- 046-212-4176
የሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ
✨ messages.ai_summary
- Procurement: Bed rental and food hospitality service for Hawassa Kenema Sport Club athletes, to be provided in a single hotel.
- Issuer: Hawassa Kenema Sport Club (Hawassa City Sport Club).
- Dates: Bid documents available for purchase for 15 consecutive days from the announcement date; submission closes on the 16th day at 3:30 AM, with opening at 4:00 AM the same day.
- Cost and bond: Bid document price 3,000 ETB; bid bond 50,000 ETB via bank-confirmed CPO or bid bond.
- Key requirements: Valid renewed trade license, business registration certificate, tax clearance proof, VAT registration, and supplier registration certificate; the competing hotel must hold a Culture and Tourism certificate of above 3 stars.
