የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለሽያጭ ክፍል አገልግሎት የሚውል የቧንቧና መገጣጠሚያ ዕቃዎችንና መፍቻዎችን እንዲሁም ጥርስ ማውጫዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለሽያጭ ክፍል አገልግሎት የሚውል የቧንቧና መገጣጠሚያ ዕቃዎችንና መፍቻዎችን እንዲሁም ጥርስ ማውጫዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት፡-
ሎት 1 ምድብ እንድ/ የቧንቧና መገጣጠሚያ ዕቃዎችና መፍቻዎች፣
- ከላይ በተጠቀሰው ዕቃ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈለ እንዲሁም በዘርፉ በቀጥታ ተሳታፊ መሆኑን የሚገልፅ ማስረጃ፣
- ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የዕቃ አቅራቢ ውስጥ የተመዘገቡ ስለመሆናቸውን የሚገልፅ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችልና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውንና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN/ መኖሩን የሚገልጽ ማስረጃ፣
- ተወዳድሮ ሲያሸንፍ ያሸነፋቸውን ዕቃዎችን በራሱ ትራንስፖርት አስከ ድርጅቱ እስቶር ድረሰ በማቅረብ የጫኝና አውራጅ ችሎ ማስረከብ የሚችል፡፡
- ከላይ በሎት አንድ /ምድብ አንድ/ የቧንቧና መገጣጠሚያ ዕቃዎችና መፍቻዎች የጨረታ ማስከበሪያ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው ከታወቁ ባንኮች ብር 50,000 /ሀምሳ ሺህ/ ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ C.P.O ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ከጨረታ ዶክመንት ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ/ ብር ከፍሎ ከድርጅቱ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በፖስታ ቴክኒካል ዶከመንት አርጅናል ለብቻ ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ እንዲሁም ፋይናንሻል ዶከመንት ኦርጅናል ለብቻ ፋይናንሻል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ አሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በአርባምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግቢ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮቻቸው በተገኙበት በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ላይ የሚከፈት ይሆናል። ሆኖም የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይንም የበዓላት ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን መዝጊያና መክፈቻ ይሆናል።
- በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም።
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ የስልክ ቁጥር 0468810369/0468812049 መደወል ይቻላል።
የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
