ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2017 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሞተር ሳይክሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2017 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሞተር ሳይክሎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም በዚህ ጨረታ መወዳደር የሚችሉት፡-
1. በመስኩ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤
2. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው፤
3. የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ያላቸው፤
የዕቃና የአገልግሎት አቅራቢነት ሰርተፊኬት ያላቸው ድርጅቶች ሀዋሳ ሲዳማ ቡና ሕንጻ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ቢሮ ቁጥር 03 በአካል መምጣት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ብር 200 እየከፈላችሁ እንድትመዘገቡና ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 10,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ CPO ወይም በባንክ የተረጋገጠ ቼክ እንድታቀርቡና የጨረታውን የመወዳደሪያ ዋጋ ኮርፖሬሽኑ ባዘጋጀው ሰነድ ላይ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ፖስታዎችን ቴክኒካል ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሻል ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ እያንዳንዳቸው ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ቢሮ ቁጥር 03 በሚገኘው የጨረታ ሳጥን እንድታስገቡ፡፡ ጨረታው በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት የጨረታ ሣጥኑ ታሽጎ በ8፡30 ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የዕረፍት ቀን ወይም የበዓል ቀን ሲሆን በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 09-16-03-72-61
ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
