አዋሽ ኢንሹራንስ ኢ.ማ. የካሣ ከፍያ ፈፅሞባቸው ከደንበኞቹ የተረከባቸውን ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎች፣ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ኢንሹራንሱ ሲገለገልባቸው የነበሩ ቀላል ተሽከርካሪዎች፣ ቁሳቁሶችንና ሌሎችንም ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
አዋሽ ኢንሹራንስ ኢ.ማ. የካሣ ከፍያ ፈፅሞባቸው ከደንበኞቹ የተረከባቸውን ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎች፣ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ዕቃዎች እና ኢንሹራንሱ ሲገለገልባቸው የነበሩ ቀላል ተሽከርካሪዎች፣ቁሳቁሶችንና ሌሎችንም ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
v በመሆኑም እነዚህን ዕቃዎች ለመግዛት የምትፈልጉ ሁሉ ቃሊቲ ከሸገር ዳቦ ጎንና ቃሊቲ ኪዳነ ምህረት ቤተከርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው የኩባንያችን የተጎዱ ተሸከርካሪዎች ማቆያ (ሪከቨሪ) በመገኘት እና በማየት የምትገዙበትን ዋጋ በታሸገ ኢንቨሎፕ ከጳጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ መስከረም 8 ቀን 2019 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡ዐዐ ሰዓት ድረስ ብሔራዊ ትያትር ጀርባ በሚገኘው አዋሽ ታወርስ የኩባንያው ዋና መ/ቤት እንግዳ መቀበያ ድረስ በመቅረብ የጨረታ ማቅረቢያ ቅጽ በመሙላት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በማስገባት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
v ጨረታው መስከረም 9 ቀን 2019 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ቃሊቲ ከሸገርዳቦ ጎን በሚገኘው የኩባንያችን ሪከቨሪ ይከፈታል፡፡
v ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም፡፡
v ተጫራቾች የመነሻ ዋጋቸው እስከ 5.000 ለሆኑት ብር 500፣ ከብር 5,001 እስከ ብር 10,000 ለሆኑት ብር 2,000 ከብር 10,001 እስከ 50,000 ለሆኑት ብር5,000 ፣ ከብር 50,000 በላይ ለሆኑት የመነሻ ዋጋውን 10% /አስር በመቶ/ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ሁሉም የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ (CPO) መቅረብ አለበት፡፡
v ተጫራቾች ከተዘጋጀው የጨረታ ማቅረቢያ ቅጽ ውጪ ሞልተው የሚያቀርቡት ማንኛውም ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታከስን ያካተተ መሆን አለበት፡፡
v በጨረታው ለተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
v ከጨረታው በኋላ ያሉትን ወጪዎች በሙሉ ገዢው ይሸፍናል፡፡
v አሸናፊዎች ንብረቶቹን ጨረታው ከተካሄደበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ከናያውን ፈጽመው ካልተረከቡ ጨረታው የሚሰረዝ _ ከመሆኑም በላይያስያዙት ገንዘብ ተመላሽ አይደረግም፣ በሌላ በኩል ክፍያ ፈፅመው ዕቃዎቹን በተገለፀው ጊዜ የማያነሱ ቢሆን ኩባንያው ኃላፊነት የለበትም፡፡
v በአዋጅ ቁጥር 681/2010 አንቀፅ 6 (3) በተደነገገው መሠረት ጥገና ለሚከናወንባቸው ተሸከርካሪዎች የተሽከርካሪው _ የባለቤትነት _ ስም እንዲዛወርለት በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከተው የመንግስት መስሪያ ቤት ማመልከት ይኖርበታል፡፡
v ኢንሹራንሱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
v ዋና መ/ቤት 01 557 00 01
v የሪቨሪ011 439 11 01
v ፋክስ 011 557 02 08
011 557 02 18
v ፖስታ ሳጥን ቁጥር 12637 አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
አዋሽ ኢንሹራንስ አ.ማ .
