Tender Detail

Tender Details

  • Company CITY GOVERNMENT OF ADDIS ABABA TRADE BUREAU (የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ)
  • Address ውቤ በረሃ ደጃች ውቤ 1888 ህንጻ 8ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 803 : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0118126179
  • Websitehttps://aacatb.gov.et/
  • Deadline06 Jan 2025, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Hotel Service Provision

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አገልግሎቶች በሎት ከፋፍሎ ግዢ ለመፈጸም የተገለፁትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተቋራጭ ተወዳዳሪዎችን ብቻ ለጨረታ ይጋብዛል።


ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ

 የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 05/2017

 

የግዥው አይነት

ሎት 1 ባለ 4 ኮከብ ሆቴል አገልግሎት ግዥ

ሎት 2 የዲጂ አገልግሎት ግዥ

  1. በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያለውና 2016 የታደሰ የንግድ የስራ ፍቃድ ያላቸው::
  2. ለእቃ አቅራቢነት ስለመመዝገባቸው እንዲሁም ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  3. የጨረታ ማስከበሪያ በእያንዳንዱ ሎት ብር 20,000 (ሃያ ብር) ወይም በባንከ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ስም CPO (ጋራንት ቢድ ቦንድ) በማሰራት ማስያዝ የሚችሉ።
  4. የጨረታ ማስከበርያ ዋስትናው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከመጨረሻው ቀን በኋላ ለተጨማሪ 28 ቀናት ፀንቶ ይቆያል::
  5. ይህ የጨረታ ማስታወቂያው ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ለእያንዳንዱ ሎት የሚይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን የአንዱ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስን ያካተተ ዋጋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ቢሮው በሰጣችሁ ፎርማት ላይ በመሙላት እና የድርጅታችሁ ማህተም ፊርማና ሙሉ አድራሻችሁን በመግለጽ፡-
    1. ፋይናንሽያል አንድ ኦርጅናል እና ፋይናንሽያስ አንድ ኮፒ
    2. ቴክኒካል አንድ ኦርጅናል እና ቴክኒካል አንድ ኮፒ በማድረግ በሰም በታሸገ በተለያዩ ፖስታዎች ማቅረብ ይኖርባችኋል፡፡
    3. ለሎት 2 ቢሮው በሚያቀርበው ዝርዝር (ናሙና) መሰረት ማቅረብ የሚችል
  7. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከሰኞ እስከ ዓርብ 230 – 1100 ሰዓት ድረስ የግዥ ዳሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 803 በዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸኋል፡፡
  8. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ 11ኛው ቀን ማለትም የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 430 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ተጫራቾች ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት (ማቅረብ) አይቻልም።
  10. ቢሮው ብዛቱን በተመለከተ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት መቀነስና መጨመር የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
  11. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 0118126179/0111703024/ በመደወል መረጃ መጠየቅ ይቻላል፡፡

አድራሻ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ውቤ በረሃ 8 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 803

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ

 

Save Tender