Tender Detail

Tender Details

  • Company የጎንደር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ
  • Address ጎንደር ከተማ : አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0581-26-03-06
  • Website
  • Deadline19 Jan 2025, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Building Construction

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ ለጎንደር ከተማ አስ/ጤና መምሪያ በማራኪ ክ/ከተማ የአየር ጤና ቀበሌ የጤና ጣቢያ አገልግሎት የሚውል የህንጻ ግንባታ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።


ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ ለጎንደር ከተማ አስ/ጤና መምሪያ በማራኪ /ከተማ የአየር ጤና ቀበሌ የጤና ጣቢያ አገልግሎት የሚውል የህንጻ ግንባታ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።

ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፡

ማቅረብ የምትችሉት መረጃዎችም፤

  1. የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
  2. የግብር መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፣
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፤
  4. የህንጻ ግንባታውን ለማሰራት ለጠቅላላ ስራ ተቋራጪ ደረጃ 7 እና ከዘያ በላይ ለህንጻ ስራ ተቋራጪ ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ የሆኑ መሆን አለባቸው፤
  5. ተጫራቾች ከላይ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  6. የሚገነባውን የግንባታ የስራ ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፤
  7. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ /ቢድ ቦንድ/ ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ላይ 1% በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /../ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ጎን//አስ/ገንዘብ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 15 መውሰድ ይችላሉ፡፡
  9. ተጫራቾች የመጫረቻ ሃሳባቸውን አንድ ወጥ በሆኑ ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በመሙላት በታሸገ ፖስታ ጎን//አስ/ግዥና/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች ዋጋውን በሚሞሉበት ወቅት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም።
  11. ተጫራቾች በሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ሙሉ ስምና ፊርማቸውን፣ የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው::
  12. ለፋይናንስ ግምገማ ያለፉት ተጫራቾች ቁጥር ቢያንስ 3 እና ከዚያ በላይ ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ የሂሳብ ስሌት /አርቲሜቲክ ቼክ/ ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 2.5% ድረስ ከሆነ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ የበለጠ ልዩነት ካጋጠመ ከውድድር ውጭ ይሆናል፤ እንዲሁም 3 በታች ከሆነ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ የሂሳብ ስሌት /አርቲሜቲክ ቼክ/ ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 1% ድረስ ብቻ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ በላይ ከሆነ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
  13. ጨረታው ክፍት ሆኖ የሚቆየው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 21 ቀናት በጎንደር /አስ/ገንዘብ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 11 በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
  14. ጨረታው 22ኛው ቀን ከጠዋቱ 400 ሰዓት ታሽጎ 4:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሆኖ ጥሪያችንን አክብረው ባይገኙም ጨረታው በሌሉበት ይከፈታል፤ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  15. ማንኛውም ተጫራች የሚቀርብ ቅሬታ ካለው ጨረታው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 የስራ ቀናት ማቅረብ የሚችል ሲሆን 5 የስራ ቀናት በኋላ የሚቀርብ ቅሬታ /ቤታችን የማይቀበል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  16. ተጨማሪ መረጃ ካስፈለገ ጎን/ከተ/አስ/ገንዘብ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 5 በአካል በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 058 126 03 06 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  17. /ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 

በአብክመ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር መምሪያ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር ቡድን

Save Tender