Tender Detail

Tender Details

  • Company የሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ
  • Address ደብረ ብርሃን ከተማ ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011-681-32-41
  • Website
  • Deadline24 Jan 2025, 10:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date
  • Categories Construction Works

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ ለቡልጋ ከተማ አስተዳደር የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የውሃ ታንከር ግንባታ ለማሠራት የሚፈልግ በመሆኑ በዘርፉ የተሠማሩና በደረጃ 5 /አምስት እና በላይ የሆኑ ህጋዊ ተቋራጭ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡


 

ብሔራዊ ግልፅ የጨረታ ‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏

የጨረታ ‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ቁጥር ፡-04/2017

 

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ ለቡልጋ ከተማ አስተዳደር የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የውሃ ታንከር ግንባታ ለማሠራት የሚፈልግ በመሆኑ በዘርፉ የተሠማሩና በደረጃ 5 /አምስት እና በላይ የሆኑ ህጋዊ ተቋራጭ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡

ተጫራቾች መሥሪያ ቤቱ ባወጣው የውሃ ታንከር ግንባታ የፍላጎት ዝርዝር መግለጫ /ቢል ኦፍ ኳንቲቲ/ መሠረት የመጫረቻ ሰነዳቸው ቴክኒካልና ፋይናንሺያል በሚል ተለይቶ አንድ ኦሪጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማቅረብ በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ መሣተፍ የሚችሉ ሲሆን ተጫራቾች በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ለመሣተፍ ማሟላት ያለባቸው ግዴታዎች፡-

  1. በዘርፉ የተሰማሩበት ህጋዊ የታደሠ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፤
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፤
  3. የግዥው መጠን ከብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ስለሚሆን የተጨማሪ እሴት ታክስ VAT ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  4. ተጫራቾች በዘርፉ የተሠማሩ ሆነው በደረጃ 2 እና በላይ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  5. ተጫራቾች በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከቴክኒካል መጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነዱን ከሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 12 ይህ ማስታወቂያ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ከወጣበት ዕለት አንስቶ እስከ 22ኛው ቀን ድረስ ዘወትር በሥራ ሠዓት የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ የሞሉትን የጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታዎች ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ ሥም ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ 60 ቀናትና እንዲሁም ለተጨማሪ 20 ቀናት ጸንቶ መቆያ ተጨምሮ በድምሩ 80 ቀናት ሆኖ መሰራት አለበት፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሠነዱን በጥንቃቄ የቴክኒካልና የፋይናንሽያል በሚል ለየብቻው አንድ ኦሪጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ በሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ የግዥና ንብ/አስ/ቢሮ ቁጥር 22 ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት‍‍‌‍‍‍‌‍‍‍‍‌‍‌‍ ማሰታወቂያው ከወጣበት ዕለት አንስቶ እስከ 22ኛው ቀን 400 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. የጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሳጥኑ 22ኛው ቀን 401 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት 430 ሰዓት በሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ መምሪያ የመሰብሳቢያ አዳራሽ የሚከፈት ሲሆን የመክፈቻው ቀን የስራ ቀን ላይ ካልዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሣሣይ ሠዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  11. /ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  12. ተጫራቾች በሌላኛው ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መጫረት አይችሉም፡፡
  13. በጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ዝርዝር መረጃ ከጨረታ‏‏‎‏‏‏‎‏‏‏‏‎‏‎‏ ሰነዱ ላይ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን በተጨማሪም ቢሮ ቁጥር 22 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 011-6-81-32-41/ 011-6-81-63 96 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡

 

የሰሜን ሸዋ ዞን ገንዘብ  መምሪያ

 

Save Tender