የጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት Desktop computer መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 0002/2017
የጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት Desktop computer መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፤
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1 እስከ 4 የተጠቀሱትንና ሌሎች ጠቃሚ ናቸው የሚሏቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር ቢሮ ቁጥር 30 ቀርበው የማይመለስ ብር 300.00 ከፍለው መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የገንዘብ መጠን ወይም ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታ ሠነዳቸው ላይ የተወዳዳሪውን ስም፣ አድራሻ፣ የሚመለከት (ህጋዊ) ወኪል የፈረመበት የተሟላና ማህተም ያረፈበት መሆኑን አረጋግጠው ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ይህ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የካላንደር ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል። የጨረታው ሳጥን በ16ኛው ቀን ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን በ10፡00 ሰዓት ላይ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የግዥ፣ ንብረትና ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬከተር የቢሮ ቁጥር 30 ይከፈታል። 15ኛው እና 16ኛው ቀን የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ቀን ላይ ከሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በ9፡30 ሰዓት ተዘግቶ ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 047 551 08 27 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን።
የጋምቤላ ሕዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ
