በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2017 ዓ.ም በጀት አመት ለቢሮና ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ ቋሚ ዕቃዎች፣ የፅህፈት መሳሪያ፣ የደንብ ልብስ፣ የፅዳት ዕቃዎች፣ አላቂ የህክምና ዕቃዎች፣ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ፣ የቧምቧ ዕቃዎችና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ሁለተኛ ዙር የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2017 ዓ.ም በጀት አመት ለቢሮና ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ ፡-
ቋሚ ዕቃዎች፣ የፅህፈት መሳሪያ፣ የደንብ ልብስ፣ የፅዳት ዕቃዎች፣ አላቂ የህክምና ዕቃዎች፣ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች ፣ የቧምቧ ዕቃዎችና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት መጫረት ይችላሉ ::
- የታደሰ የንግድ ፍቃድና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለዚህም መረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፡፡
- በመንግስት ንብረት ግዥ አስተዳደር ኤጄንሲ በዕቃ አቅራቢነት የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ (Tin) ቁጥር ሊኖራቸው ይገባል ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ በየሎቱ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ዕቃዎች ጥራትና ደረጃውን የጠበቀና ለዚህም ለእያንዳንዱ ዕቃ ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በት/ቤቱ በግ/ፋ/ን/አስ/ ቡድን (ግዥ ክፍል) ቢሮ ቁጥር 4 መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙበት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ በግልፅ በመሙላት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ከላይ በተጠቀሰው የስራ ቀናት ዘወትር የስራ ሰአት በ/ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች (ህጋዊ) ወኪሎቻቸው በተገኘበት ጨረታው በጋዜጣ በወጣበት በ11ኛው የሥራ ቀን ጠዋት 4፡00 ታሽጎ በዕለቱ ጠዋት 4፡30 ላይ በት/ቤቱ በግ/ፋ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ይከፈታል፡፡
- ት/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ ፡- ካዛንችስ ቶታል ፊት ለፈት ወደ አዋሬ መሄጃ መንገድ ምስ/ጎህ/2ኛ
ደረጃ ት/ቤት
ስልክ ቁጥር 0115-15-56-52
ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት
