አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት በአዲስ ከተማ ከፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በትምህርት፣ በጤና እና በወጣት ልማት ዘርፎች በርካታ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው:: ድርጅታችን ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ቤተሰቦች 02 (ሁለት) የመፀዳጃ ቤቶችን ማስገንባት ይፈልጋል::
የጨረታ ማስታወቂያ
አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት በአዲስ ከተማ ከፍለ ከተማ በተለያዩ ወረዳዎች በትምህርት፣ በጤና እና በወጣት ልማት ዘርፎች በርካታ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ነው::
ድርጅታችን ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ቤተሰቦች 02 (ሁለት) የመፀዳጃ ቤቶችን ማስገንባት ይፈልጋል::
በመሆኑም:-
-
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ምስከር ወረቀት ያላቸው፤
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ 2% በባንከ የክፍያ ትዕዛዝ CPO ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፤
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ወይም /Tin Number/፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስከር ወረቀት ያላቸው ወይም ከተጨማሪ እሴት ታክስ ክፍያ ነፃ ስለመሆናቸው የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው ተጫራቾች
ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 07 /ሰባት/ የሥራ ቀናት ውስጥ ክፍለ-ሃገር አውቶቡስ ተራ አዲሱ ሚካኤል አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ጽ/ቤት በመቅረብ ለዚሁ ሥራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ /መረጃ/ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ከፍለው በመግዛት የማቴሪያል ወጪ ጨምሮ የምትሰሩበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ለጨረታ ማስገቢያ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ አስገብታችሁ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ድርጅቱ ይጋብዛል::
- የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት በ8ኛው የሥራ ቀን በ3:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ4:00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል:: ስምንተኛው ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ የሚቀጥለው ሰኞ ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት ይሆናል::
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር ፡- 011-2-76-35-39/ 011-2-13-18-29/ 09-96-23-09-27
አዲስ የተቀናጀ የልማት ድርጅት
