በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ ያገለገሉ ባለ ሁለት እግር ሞተር ብስክሌት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል::
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ
ጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ ያገለገሉ ባለ ሁለት እግር ሞተር ብስክሌት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር አስራ አምስት የስራ ቀናት ውስጥ ቀርበው የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ/ በመክፈል ከመ/ቤቱ ግዥ ክፍል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ። ተጫራቾች ጨረታውን ከሞሉ በኋላ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በCPO ወይም በጥሬ ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባቸው የጨረታ ማስከበሪያ ያላስያዘ ከጨረታ ውጭ ይሆናል:: ተጫራቾች ወደ መ/ቤታችን በመቅረብ ሞተሮቹ ያሉበትን ደረጃ ዋጋ ከመሙላታቸው አስቀድሞ ማየት ይችላሉ:: ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 15 የሥራ ቀናት አየር ላይ ቆይቶ በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ በዕለቱ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል:: ሰዓቱ ከደረሰ የተጫራቾች መገኘት ወይም አለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጉልም:: ጨረታውን ያሸነፈው ተጫራች ያሸነፈውን ገንዘብ በመክፈል ተሽከርካሪዎችን በ10 ስራ ቀናት ውስጥ ማንሳት የሚችል መሆን አለበት:: ጨረታውን አሸንፎ ውጤት ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ ገንዘቡን ከፍሎ ተሽከርካሪዎችን ካላነሳ የጨረታ ማስከበሪያው ለመንግስት ገቢ ተደርጎ አሸናፊነቱ ተሰርዞ እንደገና ጨረታ የሚወጣ መሆኑን አውቆ መጫረት አለበት:: መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
046-181-40-91
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ፋይናንስ ጽ/ቤት
