የጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በስሩ የሚያስተዳድረው የእንደጋኝ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት በናሽናል ዋን ዋሽ ፕሮግራም ሾርኮ ቀበሌ ጤና ኬላ ፣ በኧሰማት ቀበሌ ጤና ኬላ እና በጀዳ ቀበሌ ጤና ኬላ ውስጥ የተሻሻለ የሽንት ቤት ግንባታ ለማስገንባት ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በስሩ የሚያስተዳድረው የእንደጋኝ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት በናሽናል ዋን ዋሽ ፕሮግራም ሾርኮ ቀበሌ ጤና ኬላ ፣ በኧሰማት ቀበሌ ጤና ኬላ እና በጀዳ ቀበሌ ጤና ኬላ ውስጥ የተሻሻለ የሽንት ቤት ግንባታ ለማስገንባት ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች በዚህ በወጣው በግልፅ ጨረታ መወዳደር ትችላላችሁ።
በመሆኑም:-
- ተጫራቾች ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የ2017 ዓ.ም ፈቃዳቸውን ያደሱ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ እና ህጋዊ ማስረጃቸውንና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች የንግድ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው::
- የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፣
- የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉና በውስጡ መካተት ያለባቸው መስፈርቶችን ያሟላ መሆን ይጠበቅበታል።
- በወረዳው ውስጥ አንድና ከአንድ ስራ በላይ ያለው ተጫራች መወዳደር አይቻልም።
- ተጫራቾች አጠቃላይ እቃ አቅርቦ የሚሰሩ መሆኑ መታወቅ አለበት።
- የጨረታ ሰነዱን ከእነደጋኝ ወረዳ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ 15,000 /አስራ አምስት ሺህ ብር/ ለእያንዳንዳቸው በእንደጋኝ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ስም በማሰራት ከኦርጂናል የጨረታ ሰነድ ጋር አብሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታ የያዘው ሰነድ ከፋ/ጽ/ቤት ከግዢ እና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የምትወዳደሩበትን ዋጋ በሚነበብ የእጅ ፅሁፍ በመሙላት ኮፒና አንድ ኦርጅናል ቴክኒካል እና ሁለት ኮፒና አንድ ኦርጅናል ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ በተለያየ ፖስታ በማሸግ በላዩ ላይ ኮፒ እና ኦርጅናል መሆኑን በመፃፍ አምስቱም በአንድ እናት ፖስታ በመጨመር በማሸግ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ አስራ አምስተኛው ቀን ድረስ 8፡00 ሰዓት ግ/ን/አስተዳደር ስ/ሂደት ቢሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል። የጨረታው ሳጥን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ8፡30 ሰዓት ይከፈታል።
ማሳሰቢያ:- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
♦ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል።
ለበለጠ መረጃ - በስልክ ቁጥር 011 350 00 47/46
በጉራጌ ዞን የእንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
