የጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በስሩ የሚያስተዳድረው የእንደጋኝ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት በናሽናል ዋን ዋሽ ፕሮግራም በላቄቾ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በዊሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እና በጀዳ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ (MHM) ክፍል ለማስገንባት ይፈልጋል፡፡
የመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ
ማስታወቂያ
የጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በስሩ የሚያስተዳድረው የእንደጋኝ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት በናሽናል ዋን ዋሽ ፕሮግራም በላቄቾ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በዊሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እና በጀዳ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ (MHM) ክፍል ለማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች በዚህ በወጣው በግልፅ ጨረታ መወዳደር ትችላላችሁ።
በመሆኑም -
- ተጫራቾች ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የ2017 ዓ.ም ፈቃዳቸውን ያደሱ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ እና ህጋዊ ማስረጃቸውንና የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የንግድ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፤
- የታከስ ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፤
- የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉና በውስጡ መካተት ያለባቸው መስፈርቶችን ያሟሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በወረዳው ውስጥ አንድና ከአንድ ስራ በላይ ያለው ተጫራች መወዳደር አይችልም፡፡
- ተጫራቾች አጠቃላይ እቃ አቅርበው የሚሰሩ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡
- የጨረታ ሰነድ ከእንደጋኝ ወረዳ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 500 /አምስት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
- በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ 15,000 /አስራ አምስት ሺህ ብር/ ለእያንዳንዳቸው በእንደጋኝ ወረዳ ፋ/ጽ/ ቤት ስም በማሰራት ከኦሪጂናል የጨረታ ሰነድ ጋር አብሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታ የያዘው ሰነድ ከፋ/ጽ/ቤት ከግዢ እና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የምትወዳደሩበትን ዋጋ በሚነበብ የእጅ ፅሁፍ በመሙላት አንድ ኮፒና አንድ ኦሪጅናል ቴከኒካል እና ሁለት ኮፒና አንድ ኦሪጅናል ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ በተለያየ ፖስታ በማሸግ በላዩ ላይ ኮፒ እና ኦሪጅናል መሆኑን በመፃፍ አምስቱም በአንድ እናት ፖስታ በመጨመር በማሸግ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ አስራ አምስተኛው ቀን ድርስ 8፡00 ሰዓት ግ/ን/ አስተዳደር ስ/ሂደት ቢሮ ማስገባት ይኖርችኋል፡፡ የጨረታው ሳጥኑ 8፡00 ታሽጎ በዚሁ እለት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 8፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ :- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
ስልክ ቁጥር -011-3-50-00-47/46
ጉራጌ ዞን የእንደጋኝ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
