አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከላይ የተጠቀሰውን ብዛታቸው 30 የሚሆኑ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-AAU/NCB/pd/03/2017/25
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ጨረታ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከላይ የተጠቀሰውን ብዛታቸው 30 የሚሆኑ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
- ተሽርካሪዎቹ የሚገኙበት አድራሻ 6ኪሎ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትራንስፖርትና ተሽከርካሪ ጥገና ክፍል ሲሆን ለመግዛት ፍላጎትና ብቃት ያላቸው ተጫራቾች በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ሰነድ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንድታቀርቡ ተጋብዛችኋል።
- ጨረታው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ሥነ- ሥርዓት መሰረት ይፈፀማል።
- ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ሀ/ በተገለፀው አድራሻ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በዩኒቨርስቲው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000087392067 ገቢ በማድረግና ደረሰኙን ይዘው በመቅረብ ስለተሽከርካሪዎቹ ሙሉ ዝርዝር የያዘውን ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ለ) በተገለጸው አድራሻ እስከ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ። የጨረታ ማስከበሪያው በተጫራቾች መመሪያ በተዘረዘረው መሰረት አያይዘው ያቀርባሉ። ዘግይተው የሚቀርቡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቁጥር 7 (ሐ) በተጠቀሰው አድራሻ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ለ) በተገለጸው አድራሻ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 4፡0o ሰዓት ወይም በፊት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የጨረታ ሰነዱን በማስገባት (በግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከጨረታ መክፈቻ ጊዜ በፊት ማቅረብ አለባቸው፡፡ ተጋባዥ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ባልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በዩኒቨርስቲው ስም አሰርተው አያይዘው ማቅረብ አለባቸው። በተጨማሪም ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ከወጣ የተያዘው የጨረታ ማስከበሪያ የሚወረስ ይሆናል።
- ሀ/ ሰነዶቹ የሚሸጡበት አድራሻ አዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 312
- ለ/ የጨረታው ሰነድ የሚገባበት አድራሻ አዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ የቀድሞ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 200
- ሐ/ ጨረታው የሚከፈትበት አድራሻ አዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ የቀድሞ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 200
- የጨረታ አሸናፊው ድርጅት የውል ስምምነት ከተፈረመበት ቀን በኋላ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ ለየኒቨርስቲው ሙሉ ክፍያ በመፈጸም ከከፈለበት ቀን ጀምሮ ባሉት በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃውን ማንሳት አለበት።
- ዩኒቨርሲቲው በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ስልክ ቁጥር 011-1-22-00-01/011-1-24-32-72 ፖ.ሣ.ቁ 1176
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ
