በማ/ኢ/ክ/መንግስት በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት ለ2017 በጀት አመት የተለያዩ ያገለገሉ መኪኖችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በማ/ኢ/ክ/መንግስት በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት ለ2017 በጀት አመት የተለያዩ ያገለገሉ መኪኖችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት መኪኖችን መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የመኪኖችን ሁኔታ አ/ው/ወ/ፋ/ፅ/ቤት ግቢ ውስጥ ማየት የሚችል መሆኑን እንገልፃለን። የመኪኖቹ አይነቶች
- ቶዮታ ደብል ጋቢና
- ላንድ ክሩዘር ሲንግል ጋቢና
በመሆኑም ተጫራቾች / ድርጅቶች
የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ለእያንዳንዱ የማይመለስ 100 ብር በመክፈል የጨረታውን ሰነድ ከአ/ው/ወ/ፋ/ፅ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 በመውሰድና በመሙላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ እንዲሁም ተጫራቾች/ድርጅቶች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ሲፒኦ ለተራ ቁጥር 1 እና 2 ለእያንዳንዳቸው 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በመሆኑም ጨረታው የሚከፈተው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከ15ኛው ቀን በኋላ ባለው የስራ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሆነ ባልተገኙበት/ከቀኑ በ6፡00 ሰአት ታሽጎ ከቀኑ በ8፡00 ሰአት በቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡
በተጨማሪም ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሰነድ አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ በፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ ፡-
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ 09-17-01-03-09 ወይም 09-11-64-83-76
በማ/ኢ/ክ/መንግስት በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፋ/ፅ/ቤት
