በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም ለወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም -5 ካፒታል በጀት የተለያዩ ግንባታ ዕቃዎችን ማቴሪያልን/ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2017 ዓ.ም ለወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም -5 ካፒታል በጀት የተለያዩ ግንባታ ዕቃዎችን ማቴሪያልን/ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በመንግሥት ግዢ አዋጅና ደንብ መመሪያ መሠረት ፡-
- የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
- የዘመኑ ግብር የተከፈለበት
- የግብር ከፋይነት ምዝገባ ቁጥር /Tin Number/
- ቫት ተመዝጋቢ የሆነ
- ከውል ዋጋ ላይ 2% የመንግስት ግብር ለመክፈል ፈቃደኛ የሆነ
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት
- EGP ኦላይን ምዝገባ መረጃ በሀርድ ኮፒ ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የጨረታ ሰነድ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማድረግ ለየብቻው በታሸገ ፖስታ ሆኖ ስማቸውን፤ ፊርማቸውን አድራሻቸውንና የሚጫረቱበትን የጨረታ ዓይነትን በትክክል ማስፈርና በማሸግ በቁ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 14 ላይ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው ጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- በጨረታ ሂደት ላይ አሸናፊ የሆነ ድርጅት ከጠቅላላው ዋጋ ላይ የውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ አለበት፣
- ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 /ሰላሳ/ የሥራ ቀናት የሚቆይ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የሥራ ዝርዝር የሚገልጸውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 /ሰላሳ/ የሥራ ቀናት በቁጫ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ድረስ በመቅረብ የተዘጋጀውን ሰነድ መግዛት የሚችሉ ይሆናል፡፡
- በጨረታ ለመሳተፍ በቅድሚያ በተዘረዘረው መሰረት ለጨረታ ዋስትና የሚሆን ቢያንስ ለ30 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ በCPO ወይም ባንክ ጋራንት ወይም ጥሬ ገንዘብ 10,000 /አስር ሺህ ብር/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው ሳጥን የሚታሸገው የጨረታው ማብቂያ በ30ኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ይሆናል።
- ጨረታው የሚከፈተው ቀጥሎ ባለው 31ኛው ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻችው በተገኘበት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ወይም የተጫራቹ ወኪል አለመገኘት የጨረታው መከፈትን አያስተጓጉልም፡፡
- በጨረታ ሂደት አሸናፊ የሆነው ድርጅት ያሸነፉበት ዕቃውን ወደ ቁጫ ወረዳ ፋ/ል/ጽ/ቤት ድረስ ጫኝ አውራጅን ጨምሮ ማድረስ አለበት ::
- ቀጥሎ ባለው 31ኛው ቀን ሰንበት ወይም በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ ፡- መ/ቤቱ ጨረታው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0464590393 ደውለው ይጠይቁ፡፡
ሞባይል ቁጥር 0917190976/0916138074
የቁጫ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት
