በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የምስራቅ ባሌ ዞን ጊንር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የተዘጋጀ የተለያየ ዕቃዎችን ግልፅ ጨረታ በማውጣት አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ፡001/2019
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የምስራቅ ባሌ ዞን ጊንር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ıኛ ዙር ግዥ በወረዳ ስር ለሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤት፤ የተዘጋጀ ደንብ ልብስ ፤ ስፌት ልብስ ፣ የፅህፈት መሳሪያ፤
የፅዳት እቃ፣ የህንፃ መሳሪያ /construction material/ ቋሚ አላቂ የቢሮ እቃዎች፣ የመኪና ጎማ እና
ባትሪ፤ ቋሚ እቃ ፈርኒቸርና ኤሌክትሮኒክስ ፣ ሞተር ሳይካሎች ባለ 150 C C እና በታችግልፅ ጨረታ በማውጣት አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የመወዳደሪያ መስፈርት
ባለው የስራ ንግድ ፍቃድ ዘርፍ ልክ የአቅራቢነት ደብዳቤ ያለው እና ማቅረብ የሚችል፤ የ2018 ግብርን ከፍሎ ያጠናቀቀ ፤ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ክሊራንስ በእያንደንዱ ያለዉን የስራ ንግድ ፍቃድ ጠቅሶ ማስረጃን ማቅረብ የሚችል ፤ ንግድ ፍቃዱን ለ2019 የስራ ዘመን ያሳደሰና ማቅረብ የሚችል የምዝገባ ቁጥር (TIN) ያለውና ማቅረብ የሚችል ።
የቫት ተመዝጋቢ የሆነ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
ማንኛውም ተጫራች ጥቃቅንና አነስተኛን ጨምሮ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ CPO 120,000 (አንድ መቶ ሃያ ሺህ ብር ብቻ/ በጊኒር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ስም አሰርተው ከcopy ቴክኒካል ሰነድ ጋር አሽጎ መቅረብ ይኖርበታል።
የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት አየር ላይ ከዋለ በኋላ በ16ኛ/ አስራ ስድሰተኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ጊኒር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥሮ 2 ይከፈታል።
ተጫራቾቹ የጨረታዉን ሰነድ በማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር ብቻ/ ከጊኒር ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ዘወትር በመንግስት የሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ:
ገዢው መስሪያ ቤት ጋር ውል ለመፈረም ፍቃደኛ የሆነ ከሚሰበስበው ታክስ 7.5 ቫትና ፐOT 3% ለመክፈል ፍቃደኛ የሆነ
ጨረታውን ተወዳድሮ ያሸነፈው ተጫራች የውል ማስከበሪያ ከተሰጠውት ትዛዝ ውስጥ 10% ማስያዝ ፍቃደኛ የሆነ።
ተጫራች ጨረታውን ማሸነፉ ከተገለፀ እና ትእዛዝ ከተቀበለ በኋላ ባሉት ተከታታይ 15 /አስራ አምስት/ የስራ ቀናት ውስጥ ጊኒር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በራሱ ትራንስፖርት ማቅረብ ይኖርበታል።
ተወዳዳሪዎች ለውድድር ሲቀርቡ ቴክኒካል copy ዶክሜንት ፣ ፋይናንሺያል ኦርጂናል ዶክሜንትና ፋይናንሽያል ዶክሜንት copy ለየብቻ በሶስት ፖስታ በሰም በኤንቨሎፕ በማሸግ ከቫት መልስ ያለውን የመወዳደሪያ ዋጋቸውን በጥንቃቄ በግልፅ በመሙላት የድርጅታቸውን ማህተም፤ ስምና ፊርማ፤ ስልክ ቁጥር አድራሻቸውን በማድረግ እንዲሁም ኦርጂናል ቴክኒካል ዶክሜንት በአጀቾ በማያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ለአሸናፊ ተወዳደሪ ክፍያ የሚፈጸመው በውድድሩ መሰረት ጥራት ያለውን እቃ በተፈለገው ጊዜ፤ መጠን፤ ቦታ፤ አይነት ሲያቀርብና በባለበጀት መስሪያ ቤቶች፤ በግዥ ኮሚቴዎች እንዲሁም በሚመለከታቸው አካላት ታይቶ ርክክብ ከተደረገና ትክክለኛ ደረሰኝ በየመስሪያ ቤቱ ከተቆረጠ በኋላ ይሆናል።
የጨረታ ሰነዱ ማቅረቢያ ጊዜ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት በ16ኛ (አስራ ስድስተኛው) የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው በዚያው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተወዳዳሪወች /ህጋዊ ወኪሎች/ ፤ የግዥ ኮሚቴዎች፤ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ባሉበት በጊኒር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በግልጽ ይሆናል።
የጨረታ ሰነዱ የሚከፈትበት ቀን ባጋጣሚ የስራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል።
የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ ዘግይቶ የሚቀርብ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
ተጫራች ይህ የጨረታ ውል ለስድስት ወር (ለግማሽ በጀት አመት/ ፀንቶ እንደሚቆይ ማወቅ ይኖርበታል።
ተጫራቾች መጫረት የሚችሉት ባላቸው የንግድ ፍቃድ ዘርፍ ብቻ መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል፤ ከንግድ ፍቃዳቸው ዘርፍ ውጭ የሚወዳደሩ ከሆነ ዋጋቸው ተቀባይነት አይኖረውም /ከጨረታ ውጭ ይሆናሉ/
Sample የተጠየቀ እቃ ላይ ሳምፕል ያላቀረበ ተጫራች የሞላው ዋጋ ተቀባይነት አይኖርም።
ተጫራች የእቃ ሞዴል የመሙላት ግዴታ አለባቸው ካልሞሉ ዋጋቸው ተቀባይነት የለውም።
ገዥው መስሪያ ቤት የግዢውን መጠን በ 20% ቀንሶ ወይም ጨምሮ ሊገዛ ይችላል።
ገዥው መስሪያ ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ይሆናል።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0913861241/0913384331
በምስራቅ ባሌ ዞን የጊንር ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
