በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለድሬዳዋ መልካ ጀብዱ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ለስራ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተዘረዘሩትን የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ለድሬዳዋ መልካ ጀብዱ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ለስራ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተዘረዘሩትን የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
|
ተ/ቁ |
የመሣሪያው ዓይነት |
ብዛት |
የፈረስ ጉልበት |
|
1 |
ቼክ ኤክስካቫተር ባለ ጃካሀመር |
1 |
|
|
2 |
ትራክ ሚክሰር |
1 |
|
|
3 |
ከርብ ስቶር ማሽን |
1 |
|
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ የኮንስትራክሽን መሳሪያ አከራይ ድርጅቶች ማሟላት ያለባችሁ መስፈርት እንደሚከተለው ይሆናል።
- የባለቤትነት መታወቂያ/ሊብሬ ያለው ወይም ህጋዊ ውክልና
- አግባብነት ያለው የታደሰ የንግድ ፈቃድና የዘመኑን ግብር የከፈለ መሆን ይኖርበታል፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፊኬት ያለው/ያላት
- የግብር ክፍያ የምስክር ወረቀት፣
- በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ፣
- የሶስተኛ ወገን ሽፋን የሚያቀርብ፣
- ነዳጅ እንዲሁም የጥገና፣ የሾፌር ደሞዝና አበል በአከራይ ይሸፈናል፡፡
- ከላይ ለተዘረዘሩት የኮንስትራክሽን መሳሪያዎች በሰዓት የሚከራይበትን ዋጋ ድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከሚገኘው ቢሯችን በአካል በመቅረብ የጨረታ ሰነድ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ መቅረብ አለበት፡፡
- በድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ስር ባሉ የስራ ቦታዎች መስራት የሚፈልግ፣
- አሸናፊ ተጫራቾች የቴክኒክ ምርመራውን ካለፈ ውል በመፈፀም ወዲያውኑ ወደ ሥራ መሰማራት አለበት።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ ቆይቶ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ድሬዳዋ በሚገኘው የመ/ቤቱ ዋና ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ዕለት የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብት አለው፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0929063249 ወይም 0919008017 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
