የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የግዥ አይነት ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የጠጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 04/2017
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የግዥ አይነት ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡
ሎት 1 የታሸገ ሚኒራል 1/2 ሊትር ውሃ ግዥ
ሎት 2 የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ
ሎት 3 የተሽከርካሪ ጥገና
በዚህ መሰረት ተጫራቾች ፡-
- በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያለውና የ 2017 የታደሰ የንግድ የስራ ፍቃድ ያላቸው::
- ለእቃ አቅራቢነት ስለመመዝገባቸው እንዲሁም ተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር በየሎቱ 30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) ወይም በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ንግድ ቢሮ ስም CPO (ጋራንት ቢድ ቦንድ) በማሰራት ማስያዝ የሚችሉ።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትናው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከመጨረሻው ቀን በኋላ ለተጨማሪ 28 ቀናት ፀንቶ ይቆያል::
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን የአንዱ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታከስን ያካተተ ዋጋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ቢሮው በሰጣችሁ ፎርማት ላይ በመሙላት እና የድርጅታችሁ ማህተም፣ ፊርማና ሙሉ አድራሻችሁን በመግለጽ
- ፋይናንሽያል አንድ ኦርጅናል እና ፋይናንሽያል አንድ ኮፒ
- ቴክኒካል አንድ ኦርጅናል እና ቴክኒካል አንድ ኮፒ በማድረግ በሰም በታሸገ በተለያዩ ፖስታዎች ማቅረብ ይኖርባችኋል፡፡
- ለሎት 1 ለምትወዳደሩበት ውሃ አንድ (01) ፍሬ ናሙና (ሳምፕል) ማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከሰኞ -ዓርብ ከ2:30 -11፡00 ሰዓት ድረስ የግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 803 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸኋል፡፡
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ በ11ኛው ቀን ማለትም የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወደም ሀጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ተጫራቾች ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት (ማቅረብ) አይቻልም፡፡
- ቢሮው ብዛቱን በተመለከተ በጨረታ ሰነዱ ላይ በገለፅነው መሰረት መቀነስና መጨመር የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118126179/0111703024/ በመደወል መረጃ መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ውቤ በረሃ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 803
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ
