ብራና ማተሚያ ድርጅት የተለያዩ አይነት የህትመት ጥሬ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 008/2017
ብራና ማተሚያ ድርጅት የተለያዩ አይነት የህትመት ጥሬ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሠረት በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች በማሟላት መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡
1ኛ በዘርፉ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ምዝገባ ማቅረብ የሚችሉ፣
2ኛ የዘመኑን ግብር የከፈሉና ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
3ኛ የግብር ከፋይነት መለያ ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
4ኛ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ሠርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
5ኛ ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለሥልጣን ጨረታ ላይ መሳተፍ እንዲችሉ የተሰጠ ክሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
6ኛ በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ በአቅራቢነት ለመመዝገባቸው ማስረጃ ያላቸው፣
7ኛ ተጫራቾች ለጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር አምስት መቶ (500.00) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት (ቅዳሜ ግማሽ ቀንን ጨምሮ) ወሎ ሰፈር በሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 32 በአካል በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
8ኛ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ያቀረቡትን ዋጋ 2% በሲፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
9ኛ ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የማስረከቢያ ጊዜ መጥቀስ አለባቸው፣
10ኛ ተጫራቾች በጨረታው ያሸነፏቸውን ዕቃዎች ድርጅቱ መጋዘን ድረስ ማድረስ አለባቸው፣
11ኛ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ11ኛው የሥራ ቀን እስከ 8፡00 ሰዓት (ከሰዓት) ድረስ በሰም በታሸገ ፖስታ ለጨረታ ማስገቢያ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በእለቱ 8፡00 (ከሰዓት) ታሽጎ 8፡30 (ከሰዓት) በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
12ኛ ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ ፦ ከወሎ ሰፈር ወደ ጎተራ በሚወስደው መንገድ 700 ሜትር ላይ በስተግራ በኩል
ብራና ማተሚያ ድርጅት
