የአዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም በጀት ለ2ኛ ዙር ለሥልጠና የሚውል የስቴሽነሪ፣ የኤሌክትሪክ/ ኤሌክትሮኒክስ፣ የኮንስትራክሽን፤ የጋርመንት፣ የአውቶሞቲቭ፣ ለሆቴል እና ለውበት ሳሎን ማሠልጠኛ የሚውሉ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም በጀት ለ2ኛ ዙር ለሥልጠና የሚውል የስቴሽነሪ፣ የኤሌክትሪክ/ ኤሌክትሮኒክስ፣ የኮንስትራክሽን፤ የጋርመንት፣ የአውቶሞቲቭ፣ ለሆቴል እና ለውበት ሳሎን ማሠልጠኛ የሚውሉ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ፦
-
በሥራ መስኩ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
-
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ወይም ለመክፈላቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ፣
-
የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
-
የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣
-
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረ ቼከ (CPO) ማስያዝ አለባቸው፡፡
-
የአንድ ሰነድ ዋጋ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በመግዛት በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ብቻ ዋጋ በመሙላት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ኮሌጁ ለዚህ ጨረታ ባዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው:: ሳጥኑ በ11ኛው ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዛው ዕለት በ9፡00 ሰዓት ይከፈታል፡፡
-
ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ቫት ያካተተ መሆን አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ የቀረበው ዋጋ ቫት ያካተተ እንደሆነ ተቆጥሮ ይወሰዳል፡፡
-
የሽያጫችሁን ቫት 7.5% እና ዊዝ ሆልድ 2% የሚቆረጥ መሆኑን ልብ ይበሉ፡፡
-
የጨረታው አሸናፊ በጨረታው ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች እስከ በጀት አመቱ መጨረሻ ሲታዘዝ ኮሌጅ ድረስ በራሱ ወጭ ማቅረብና የዕቃው ጥራት በተጠቃሚ ባለሙያ ሲረጋገጥ ብቻ ርክክብ የሚደረግና ክፍያ የሚፈጸም ይሆናል፡፡
-
ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ ስ.ቁ 0221115245 ደውለው ማነጋገር ይችላሉ፡፡
አድራሻ ፡- አዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዳማ ከተማ ቀበሌ ደደቸ አራራ (04)
በኦሮሚያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ሙያ ቢሮ የአዳማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
