የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የፈርኒቸር እና ነዳጅና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ፡፡
የዕቃ ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የፈርኒቸር እና ነዳጅና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ፡፡ ስለዚህ መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡
-
በዘርፍ ህጋዊ ንግድ ፊቃድ ያላቸው ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣ የግብር ከፋይ ቁጥር (TIN No) ያላቸው ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፣ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ
-
አቅራቢነት ማስረጃ ኦን ላይን ማቅረብ የሚችል ፣
-
ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ጨረታ 40,000.00 /አርባ ሺህ ብር/ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ እና ከጨረታው ማስከበሪያ የምፈቅደውን ማስያዝ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል፡፡
-
ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ለ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአ/ም/ከ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ በመቅረብ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነድ እንድትገዙ እንገልፃለን ፡፡
-
ዋጋቸውን በማያሻማ መልኩ እንድታቀርቡ እናሳውቃለን ፡፡
-
የጨረታ ሣጥን የሚታሸገው በዕለቱ ከረፋዱ 4፡00 ሲሆን የሚከፈተው 4፡30 በከተማው በፋ/ጽ/ቤት ይሆናል፡፡ ዕለቱ በዓል ወይም ዕረፍት ከሆነ በቀጣይ ቀን ይሆናል፡፡
-
ተጫራቾቹ ጨረታ ዶክመንት /አንድ ኦርጅናልና አንድ ቴክኒካል ኮፒ 1 እና 2 ኮፒ ፋይናንሻል ኦርጅናል እና አንድ ፋይናንሻል ኮፒ 1 እና ኮፒ 2 እንዲሁም CPO በፖስታ አድርገው በእናት ፖስታ አሽገው እንዲያቀርቡ ይፈልጋል፡፡
-
ውል ማስከበሪያ ማስያዝ የሚችል፤
-
አሸናፊው ዕቃውን የሚያስረክብበት ቦታ በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ሲሆን ማስጫኛና ማውረጃ የትራንስፖርት ወጪዎች በአሸናፊው ይሸፈናል፡፡
-
አሸናፊው ድርጅት ያሸነፏቸውን ዕቃዎች ናሙና የማቅረብና የማስያዝ ግዴታ አለበት፡፡
-
በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
-
የዕቃው መጠን በሰነዱ ላይ በተገለፀው መሠረት በ20% ሊጨምርም ሆነ ሊቀንስ ይችላል፡፡
-
መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክ/መ/ በጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ /ጽ/ቤት
